Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየመምህር ግርማ ቤት ተበረበረ

የመምህር ግርማ ቤት ተበረበረ

ቀን:

በማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት መምህር (አጥማቂ) ግርማ ወንድሙ፣ አያት የሚገኘው መኖርያ ቤታቸው በፖሊስ መበርበሩ ታወቀ፡፡

ፖሊስ ቤታቸውን ሲበረብር ያገኘው ነገር ባይገለጽም፣ ለተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ማስረጃ የሚሆነውና ሌሎች ተጨማሪ ነገሮች ፍለጋ ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

መምህር ግርማ ከሁለት ወራት በፊት የእስር ትዕዛዝ ተሰጥቶባቸው እንደነበር ተጠቁሞ፣ አንድ ቀን ፖሊስ ጣቢያ አድረው ጥቅምት 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ በወቅቱም ፖሊስ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸው ነበር፡፡ የፖሊስን ጥያቄ በመቃወም የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ከእስር እንዲፈቱ በጠበቃቸውና በራሳቸው የጠየቁ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ አልተቀበላቸውም፡፡

መምህር ግርማ የተጠረጠሩበትን የማታለል ወንጀል የፈጸሙት፣ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም. እንደሆነና በየካ ክፍለ ከተማ ወሰን ግሮሰሪ አካባቢ ነዋሪ መሆናቸው ከተጠቆመው አቶ በላይነህ ከበደ መኖርያ ቤት ጋር የተገናኘ መሆኑ በምርመራው ተገልጿል፡፡

ፖሊስ በምርመራው እንዳረጋገጠው አቶ በላይነህ ከትዳር አጋራቸው ጋር የሚኖሩበት በ400 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ መኖርያ ቤት ነበራቸው፡፡ አቶ በላይነህ ቤታቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ካልሸጡ ሊሞቱ እንደሚችሉ መምህር ግርማ ሲነግሯቸው፣ ከፍተኛ ዋጋ ያወጣላቸው የነበረ ቤታቸውን በ800 ሺሕ ብር ለመሸጥ መገደዳቸውን የፖሊስ ምርመራ ይጠቁማል፡፡

መምህር ግርማ ቤቱን ማሸጥ ብቻ ሳይበቃቸው፣ ገንዘቡ እንዲበረክትላቸው እንዲፀለይበት እንዲሰጧቸው የተጠየቁት አቶ በላይነህ፣ ገንዘቡን መስጠታቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቷል፡፡ ሊፀለይበት ወደ መምህር ግርማ ቤት ተወስዷል የተባለው ገንዘብ ውሎ በማደሩ፣ አቶ በላይነህ ወደ መምህር ግርማ ቤት ስልክ ሲደውሉ ስልኩ አልሠራ እንዳላቸውና ወደ ውጭ አገር መሄዳቸውን እንደሰሙ መግለጻቸው በፖሊስ ተጠቅሷል፡፡

ተጠርጣሪው መምህር ግርማ ለፍርድ ቤቱ ከሳሻቸውን ቀይ ይሁኑ ጥቁር እንደማያውቋቸውና ሆን ተብሎ የተሸረበባቸው ሴራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና የማያስከለክል መሆኑን በመግለጽ በዋስ እንዲለቀቁ ቢጠይቁም፣ ፍርድ ቤቱ አልተቀበላቸውም፡፡ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ባለመቀበል ሰባት ቀናትን በመፍቀድ ለጥቅምት 25 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...