Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናኢሕአዴግ ዓብይ አህመድን (ዶ/ር) ሦስተኛው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

ኢሕአዴግ ዓብይ አህመድን (ዶ/ር) ሦስተኛው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

ቀን:

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) ምክር ቤት ከማክሰኞ መጋቢት 11 ቀን 2010 .. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ባደረገው ስብሰባ የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ሊቀመንበር የሆኑትን ዓብይ አህመድን (ዶ/ር) የግንባሩ ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ፡፡

ምክር ቤቱ የኢሕአዴግ ሦስተኛውን ሊቀመንበር ከመምረጡ በፊት የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝን የሥራ መልቀቂያ በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አፅድቆታል፡፡ ከሊቀመንበርነት ምርጫ በፊት ምክር ቤቱ የአራቱ የግንባሩ አባል ድርጅቶችን የጥልቅ ተሃድሶ ግምገማ ሪፖርት አዳምጦ ሰፋ ያለ ውይይት አድርጎበታል፡፡

ከምክር ቤቱ አስቀድሞ በተደረገው የኢሕአዴግ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ የአራቱን አባል ድርጅቶች ግምገማጥልቀት ገምግሞ ከጨረሰ በኋላ፣ ለምክር ቤቱ የሚያቀርበውን የመወያያ ሰነድ መዘጋጀቱን  የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) ሊቀመንበር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ተናግረው ነበር፡፡ በወቅቱ በምክር ቤቱ የጠቅላይ ሚኒስትርና የግንባሩ ሊቀመንበር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መልቀቅ የፈጠረውን የአመራር ክፍተት ለመድፈን፣ የአመራር መተካት እንደሚኖር አመላክተው ነበር፡፡

በኢሕአዴግ የተለምዶ አሠራር የፓርቲው ሊቀመንበር የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆን ስለሚታወቅ፣ ተመራጩ ሊቀመንበር በፓርላማ እንደሚሰየም ይጠበቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኦቲዝምን ለመቋቋም በጥምረት የቆሙት ማዕከላት

ከኦቲዝም ጋር የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ...

አወዛጋቢው የወልቃይት ጉዳይ

የአማራና ትግራይ ክልሎችን እያወዛገበ ያለው የወልቃይት ጉዳይ ዳግም እየተነሳ...

ተጠባቂው የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የውድድር መለኪያ የሆነው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በኢትዮጵያ

የሞባይል ገንዘብ ዝውውር የሞባይል ስልክን በመጠቀም ሊገኙ የሚችሉ የፋይናንስ...

የአማራና ደቡብ ክልሎች ለሠራተኛ ደመወዝ መክፈል መቸገራቸውን የፓርላማ አባላት ተናገሩ

በአማራና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት...