Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበሱዳን ሲካሄድ የነበረው የሚኒስትሮች ስብሰባ ያለውጤት ተበተነ

በሱዳን ሲካሄድ የነበረው የሚኒስትሮች ስብሰባ ያለውጤት ተበተነ

ቀን:

የኢትዮጵያ፣ የግብፅና የሱዳን የውጭ ጉዳይና የውኃ ሀብት ሚኒስትሮች በህዳሴ ግድቡ ውኃ አሞላልና አለቃቀቅ እንዲሁም የግድቡን አካባቢያዊ ተፅዕኖን በተመለከተ በሱዳን ካርቱም ከመጋቢት 26 እስከ 27 ቀን 2010 ዓ.ም. ሲካሄድ የነበረው ስብሰባ ያለውጤት ተጠናቀቀ፡፡

ሪፖርተር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ማረጋገጥ እንደቻለው፣ ስብሰባው ሊቋረጥ የቻለው በዓባይ ውኃ ክፍፍል ላይ ከግብፅ በተነሳ ጥያቄ ምክንያት ነው፡፡

በጥር 21 ቀን 2010 ዓ.ም. በመሪዎች ደረጃ የተሰጠውን መመርያ ለመተግበር የሚቻልበት ሁኔታ እንዲፈጠር ኢትዮጵያ ጥረት ስታደርግ መቆየቷን የጠቆሙት ኃላፊው፣ ግብፅ አሁንም እ.ኤ.አ. የ1959 የውኃ አጠቃቀም ስምምነት የውይይቱ አካል እንዲሆን ጽኑ አቋም በመያዟ መሰናክል መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ስብሰባውን በቀጣይ ለማካሄድ ስምምነት ቢኖርም፣ መቼ እንደሚካሄድ ግን እርግጠኛ የሆነ የጊዜ ቀጠሮ አልተያዘለትም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...