Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ የተሰጠው ውሳኔ ታገደ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ የተሰጠው ውሳኔ ታገደ

ቀን:

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በመከላከያ ምስክርነት ስለመቅረባቸውና አለመቅረባቸው ትርጉም እንደሚሰጥበት በማስታወቅ፣ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ አገደው፡፡

በሽብር ተግባር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ በተመሠረተባቸው እነ ዘመኑ ካሴ መዝገብ፣ በመከላከያ ምስክርነት መቅረብ እንዳለባቸው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ ያገደው ሰበር ሰሚ ችሎቱ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 123 (ሀ) አንፃር መከላከያ ምስክር መሆን ስለሚችሉበት ወይም ስለማይችሉበት ሁኔታ መርምሮ፣ የሕግ ትርጉም ሊሰጥበት እንደሚገባ ጠቁሟል፡፡

ሕጉ እንደሚያብራራው ወንጀለኛው ከሕዝባዊ መብቶቹ ማለትም ከመራጭነት፣ በምርጫ ተካፋይ ከመሆንና ለሕዝብ አገልግሎት ሥራ ከመመረጥ፣ ለማዕረግ ከመመረጥ፣ በሰነድ ወይም በውል ስምምነት ላይ ምስክር ወይም ዋስ ከመሆን፣ ለፍርድ ሥራ ልዩ አዋቂ ሆኖ ከመሥራት መብቱ መሻሩን ይገልጻል፡፡

ችሎቱም ከላይ በተጠቀሰው ሕግ ላይ ትርጉም መስጠት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው መከላከያ ምስክር መሆን እንደሚችሉ አስታውቆ፣ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የሰጠውን ብይን በማፅደቅ የዓቃቤ ሕግን አቤቱታ ውድቅ ያደረገበት ውሳኔ ሳይፈጸም እስከ ጥር 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ታግዶ እንዲቆይ አዟል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...