‹‹ለራሴና ለፊፋ ስል እፋለማለሁ››
የፊፋ ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላተር፣ የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) የሥነ ምግባር ኮሚቴ፣ እሳቸው ከአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር ፕሬዚዳንት ሚሼል ፕላቲኒ ጋር የፊፋን የሥነ ምግባር መርሆች በመቃረን በ‹‹አግባብ ያልሆነ ክፍያ›› ጥፋተኛ ናችሁ በማለት ለስምንት ዓመት መታገዳቸውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የተናገሩት፡፡ ሁለቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከዚህ ቀደም ከፊፋ ካዝና ወጥቶ ለሚሼል ፕላቲኒ እ.ኤ.አ. በ2011 በተከፈለ ሁለት ሚሊዮን ዶላር ጉዳይ ተከሰው ለሦስት ወራት ታግደው ነበር፡፡ ከካዝና የወጣው ገንዘብ ፕላቲኒ ለብላተር በአማካሪነት ላገለገሉበት የተከፈለ ነው ሲሉ ተወንጃዮቹ አስተባብለዋል፡፡