Thursday, June 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየወረገኑ ተፈናቃዮች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታ አቀረቡ

የወረገኑ ተፈናቃዮች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታ አቀረቡ

ቀን:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ሕገወጥ የመሬት ወረራ አካሂደዋል” በማለት ያፈናቀላቸው የወረገኑ አባወራዎች ጠቅላይ ሚኒስተር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መፍትሔ እንዲሰጧቸው  አቤቱታ አቀረቡ፡፡

የወረገኑ ተፈናቃዮች ያቋቋሙት ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ ማክሰኞ ሚያዝያ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ በላከው ደብዳቤ፣ በአጠቃላይ የተፈናቀሉት ከ25 ሺሕ በላይ ናቸው ብሏል፡፡

“ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮ የሚገፋ ነዋሪ መኖሪያ ቤቱ ፈርሶ ጎዳና ላይ ወድቋል፤” በማለት የሚገልጸው የአቤቱታ ደብዳቤው፣ “ተማሪዎችም ትምህርት ለማቋረጥ ተገደዋል፤” ይላል፡፡

‹‹ቤት የፈረሰብን ዜጎች በተለያዩ ጊዜያት ከአርሶ አደሮች በሕጋዊ ውል ቤት የገዛን ብንሆንም፣ የአርሶ አደሮችን ቤት በመተው ከአርሶ አደር የገዛነውን ቤት በማፍረስ ማፈናቀል አግባብ አይደለም፡፡ ሆን ተብሎ እኛን ብቻ ለማፈናቀል ታስቦ የተደረገ ከፋፋይ ሴራ ነው፤” በማለት ኮሚቴው ገልጾ፣ በ2005 ዓ.ም. የኮንዶሚንየም ምዝገባ በሚካሄድበት ወቅት ሕጋዊ ስለምትደረጉ አትመዝገቡ በመባላቸው ተደራራቢ በደል እንደደረሰባቸው ኮሚቴው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፈው አቤቱታ አስረድቷል፡፡

በአሁኑ ወቅት ተፈናቃዮች ኑሮ እንደ ከበዳቸው፣ ሕፃናት፣ አቅመ ደካሞች፣ አካል ጉዳተኞችና ነፍሰ ጡሮች ለከፍተኛ ችግር እየተዳረጉ መሆኑን በመጥቀስ መንግሥት መጠለያ እንዲሰጣቸው ተፈናቃዮቹ በኮሚቴያቸው አማካይነት ጠይቀዋል፡፡

በ2008 ዓ.ም. ክረምት መባቻ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ መዋቅሮችን አስተባብሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ወረገኑ አካባቢ፣ እንዲሁም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍል ከተማ ወረዳ 1 አካባቢ ሕገወጥ የመሬት ወረራ አካሂደዋል ያላቸውን ነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች በኃይል ማፍረሱ አይዘነጋም፡፡

ከዚያ ጊዜ ወዲህ በተለይ የወረገኑ ተፈናቃዮች ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤትና ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ተደጋጋሚ ቅሬታ ቢያቀርቡምና ለቅሬታቸው ምላሽ እንደሚሰጥ ቢገለጽላቸውም፣ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኙ ለጠቅላይ ሚኒስተሩ በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...