Tuesday, December 5, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትኢትዮጵያ በሪዮ ኦሊምፒክ በውኃ ዋና የመወከል ዕድል አገኘች

ኢትዮጵያ በሪዮ ኦሊምፒክ በውኃ ዋና የመወከል ዕድል አገኘች

ቀን:

ኢትዮጵያ በመጪው ክረምት በብራዚል በሚካሄደው የሪዮ ኦሊምፒክ በሚኒማ ከምትሳተፍባቸው ስፖርቶች በተጨማሪ በውኃ ዋና በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት ተወዳዳሪዎች የምትወከልበት ዕድል ማግኘቷ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳንኤል አበበ ለሪፖርተር እንደገለጹት ከሆነ፣ ኢትዮጵያ ይህንን ዕድል ያገኘችው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ)፣ በዝቅተኛ የተሳትፎ ደረጃ ላይ የሚገኙ አገሮች በውኃ ዋና ያለሚኒማ ዓለም አቀፍ ተሳትፎን ለማረጋገጥ የተገኘ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው የሪዮ ዲጄኔሮ ኦሊምፒክ ተሳትፎን አስመልክቶ ከሳምንት በፊት በሰጠው መግለጫ ኢትዮጵያ በአራት የስፖርት ዓይነቶች ማለትም በአትሌቲክስ፣ በብስክሌት፣ በወርልድ ቴኳንዶና በቦክስ እንደምትወከል፣ በተሳትፎዋም አራት የወርቅ፣ አራት የብርና አራት የነሐስ በድምሩ 12 ሜዳሊያዎችን ለማግኘት ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን መናገሩ ይታወሳል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...