መቀመጫውን በፈረንሣይ ፓሪስ ያደረገው የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ማክሰኞ ታኅሳስ 29 ቀን 2008 ዓ.ም. ካወጣው መግለጫ የተወሰደ፡፡ በድርጅቱ መግለጫ መሠረት በዓለም ዙሪያ ከተገደሉ ጋዜጠኞች ውስጥ 67 ያህሉ ሥራቸውን በማከናወን ላይ እያሉ የተገደሉ ናቸው፡፡ ግድያቸውም ሆን ተብሎ የተፈጸመ ነው፡፡ በድርጅቱ ሪፖርት እንደተገለጸው 43 ጋዜጠኞች በምን ምክንያት እንደተገደሉ ግልጽ አልሆነም፡፡ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ማርጋሽ ኤው እንዳሉት፣ ምክንያቱ ባይታወቅም በሥራቸው ምክንያት ዒላማ መሆናቸው ግን አይስተባበልም፡፡ ከእነዚህ መደበኛ ጋዜጠኞች በተጨማሪ 34 የማኅበራዊ ሚዲያ ጋዜጠኞች እ.ኤ.አ. በ2015 መገደላቸውን ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2005 ጀምሮ በአጠቃላይ 787 ጋዜጠኞች በተለያዩ አገሮች መገደላቸው በሪፖርቱ ተጠቁሟል፡፡ ዘንድሮ ኢራቅና ሶሪያ በጋዜጠኞች ግድያ በመጀመርያዎቹ ረድፍ ላይ ሲገኙ፣ ስምንት ጋዜጠኞች የተገደሉባት ፈረንሣይ በሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡