Wednesday, March 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍርፍሬከናፍር

ፍሬከናፍር

ቀን:

ሚኒስትር ሐሳብ አመንጪ እንጂ አቃቂር አውጪ አይደለም!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በጽሕፈት ቤታቸው ለመንግሥት ከፍተኛ ሹማምንት በሥራዎቻቸውናአሠራራቸው ዙሪያ ግንቦት 7 ቀን 2010 ዓ.ም. ገለጻና ማሳሰቢያሰጡበት አጋጣሚ የተናገሩት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም ከእንግዲህ እያንዳንዱ ሚኒስትር ለካቢኔ ስብሰባ ሲመጣ በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባውም ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ዓቢይ ከስብሰባው በኋላ ሹማምንቱን ከአዳራሽ ይዘው በመውጣት በዳግማዊ አፄ ምኒልክ፣ በቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴና በዘመነ ደርግ የተለያዩ ታሪካዊ ድርጊቶች የተፈጸሙባቸው በታላቁ ቤተ መንግሥት የሚገኙና ዝግ የነበሩ የተለያዩ ክፍሎችን አስከፍተው እንዲጎበኟቸው ማድረጋቸውን፣ በዚህም አጋጣሚ የነገሥታቱን የግብር ቤቶች፣ አፄ ኃይለ ሥላሴ የተገደሉበትንና የደርግ ጄኔራሎች የተረሸኑባቸውን ክፍሎች በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት መገበኘታቸው ታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...