Sunday, December 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየፊፋ የሥነ ምግባር ኮሚቴ ምርምራ ቀጥሏል

የፊፋ የሥነ ምግባር ኮሚቴ ምርምራ ቀጥሏል

ቀን:

ፈረንሣዊው የፊፋ ዋና ጸሐፊ ተባረሩ

ከታላላቅ መንግሥታት ተፅዕኖ ሳይቀር ገለልተኛ ሆኖ በአይነኬነቱ ለዓመታት የዘለቀው የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) በተቋሙ ውስጥ የተንሰራፋውን የሙስና ቅሌት እየመረመረ የሚገኘው የፊፋ ሥነ ምግባር ኮሚቴ ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ፈረንሣዊው የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክን አሰናብቷል፡፡

ከሁለት አሠርታት በላይ የፊፋን የፕሬዚዳንትነት ሥልጣን ያለተቀናቃኝ ጨብጠው እስከ 2015 መጨረሻ ድረስ የቆዩት ሲዊዘርላንዳዊው የዕድሜ ባለፀጋው ሴፕ ብላተርና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር (ዩኢኤፍኤ) ፕሬዚዳንት ሚሸል ፕላቲኒ በዚሁ ከፊፋ ጋር ተያይዞ ሲነገር በቆየው የሙስና ቅሌት ተዘፍቀው ስለተገኙ የስምንት ዓመት ዕገዳ ተላልፎባቸው መሰናበታቸው ይታወሳል፡፡

አሁን ደግሞ የፊፋ ዋና ጸሐፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትና የ55 ዓመቱ ፈረንሣዊው ዠሮም ቫልክ የሥነ ምግባር ኮሚቴው እ.ኤ.አ. ጥር 13 በዙሪክ ባደረገው ስብሰባ እንዲታገዱ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ መክንያት ያለው ደግሞ በ2010 እና በ2014 የዓለም ዋንጫ ዝግጅት ወቅትና በተለይ ደግሞ ኮንፌዴሬሽን ኦፍ ኖርዝ ሴንትራል አሜሪካ ኤንድ ካሪቢያን አሶሴሽን ፉትቦል (ሲኦኤሲኤሲኤኤ) አዘጋጅ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ለነበሩት ጃክ ዋርነር ተሰጥቷል ተብሎ በሥነ ምግባር ኮሚቴው ይፋ የተደረገው የአሥር ሚሊዮን ዶላር ጉዳይ ስለመሆኑ ተዘግቧል፡፡ ቀጣዩ የፊፋ ምርጫ በሚቀጥለው ወር እንደሚከናወንም ተነግሯል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...