- Advertisement -

ከኃላፊነት የሚነሱ ባለሥልጣናትን በአምባሳደርነት መሾም በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሥልጣን ጊዜያቸውን ጨርሰውም ሆነ ሳይጨርሱ ከኃላፊነት የሚነሱ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ ባለሥልጣናት በአምባሳደርነት የሚሾሙበትን አሠራርና የፍትሐዊነት ችግር በተመለከተ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ተነሳ፡፡

ጥያቄው የተነሳው ሐሙስ ግንቦት 8 ቀን 2010 ዓ.ም. የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) የመሥሪያ ቤታቸውን የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ሲያቀርቡ ነው፡፡ ሪፖርቱ ከቀረበ በኋላ በፓርላማው የውጭ ግንኙነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበርካታ ጉዳዮች ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡ በውጭ አገሮች በኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና የቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች የሚመደቡ ዲፕሎማቶች ያላቸው ክህሎት፣ ዕውቀት፣ አሿሿምና ተሿሚ ዲፕሎማቶች የሚመደቡባቸውን አገሮች የጥቅም ግጭትና ፍትሐዊነትን በተመለከተ፣ የቋሚ ኮሚቴው አባል በሆኑት በአቶ ዘለቀ መሐሪ የቀረቡት ይገኙበታል፡፡

‹‹የአገራችን የዲፕሎማሲ ሥራዎች ከሚከናወኑባቸው መንገዶች አንዱ፣ ከአገር ጥቅም አኳያና ከስትራቴጂካዊ ወዳጅነት አንፃር በየአገሮች ሚሲዮኖች መክፈት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ለኤምባሲዎች የሚመደቡ አምባሳደሮች ወቅቱ ከሚጠይቀው የዓለም ተለዋዋጭ ሁኔታ አኳያ፣ የቢዝነስ ዲፕሎማሲውን ለማሳለጥና የአገሪቱን ጥቅም ከማስጠበቅ አንፃር፣ ባላቸው ብቃትና ክህሎት መሠረት አድርጎ መሾም ሲገባ፣ አንዳንዶቹ አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶችን ሲመሩ ውጤታማነታቸው ጥያቄ ውስጥ የገባ ነበሩ፡፡ እነዚህን ተሿሚዎች ወይ በጡረታ መሸኘት፣ ወይም ሌላ ቦታ መመደብ ሲገባቸው በአምባሳርነት መመደቡ፣ በዲፕሎማሲ ሥራ  የአርን ጥቅምና ገጽታ ከማስቀደም አኳያ በብቃትና በልምድ ላይ ያልተመሠረተ ሹመት ለምን ያስፈልጋል?›› የሚሉ ጥያቄዎች ለሚኒስትሩ ቀርቦላቸዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው አባል የተሿሚ ዲፕሎማቶችን (አምባሳደሮችን) በስም ባይጠቅሱም፣ ባልና ሚስት በአንድ ሚሲዮን ስለመመደባቸውም ተጨማሪ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ለአብነትም በካናዳና በብራሰልስ (ቤልጂየም) የተመደቡ ዲፕሎማቶችን ማየት እንደሚቻል ጥያቄውን ያቀረቡት አቶ ዘለቀ፣ ወቅቱ ከሚጠይቀውና ከዲፕሎማሲ ውጤትና ከአዋጁ አንፃር እንዴት እንደሚታይ የሚኒስትሩን ማብራሪያ ጠይቀው ነበር፡፡

ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ሚኒስትሩ ወርቅነህ (ዶ/ር)፣ የአምባሳደሮቹ ምድባ በትምህርትና በብቃት ላይ ተመሥርቶ ብቻ መሆን አለበት የሚለውን እንደሚቀበሉት ገልጸዋል፡፡ የአምባሳደርነት አመዳደቡ በሁለት ዓይነት መንገድ እንደሚከናወን ያስረዱት ሚኒስትሩ፣ አንደኛው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከታች እርከን ጀምሮ የሚያበቃቸውን ሠራተኞች በመምረጥ ሲሆን፣ ሌላው በመንግሥት ከተለያዩ ተቋማት ለሚመጡ ምደባ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን በነበረው አሠራርም ቢሆን በተመደቡ አምባሳደሮች የአገሪቱን ፍላጎት በማሳካት ረገድ የታየ ችግር አልነበረም ብለዋል፡፡

‹‹በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ተመድበው በአመራር ላይ የነበሩት ሚኒስትሮች ሆኑ ሌሎች ኃላፊዎች ለአምባሳደርነት ሲታጩ፣ በፊት የነበራቸውን ልምድና የአመራር ዕውቀት ይዘው ነው የሚመጡት፡፡ የአገሪቱን ፍላጎትና ጥቅም፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ የሚያውቁ በመሆናቸው መጠነኛ ሥልጠና በመስጠት የሚመደቡበት አሠራር ያለ ሲሆን፣ የአገሪቱን ጥቅምና ፍላጎት በዲፕሎማሲው መስክ ሊያሳኩ እንደሚችሉ ስለሚታመንባቸው ነው፤›› ብለዋል፡፡

- Advertisement -

ነገር ግን ይኼ አሠራር በምክር ቤቱ አባላት ብቻ ሳይሆን በሕዝቡም ውስጥ እየተነሳ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ወደፊት ግን በብቃትና በክህሎት ላይ ተመሥርቶ ግልጽ የሆነ የአሠራር መመርያ እንደሚያስፈልግና ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አሠራሩን ለማስፈጸም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

በተሿሚ ዲፕሎማቶች ባልና ሚስት አመዳደብ ላይ የአድሎዓዊነት ጥያቄ  ስለመኖሩና ሁለት ዲፕሎማቶች አንድ ቦታ ስለመመደባቸው በተመለከተ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ እንዳስረዱት፣ ሁለት ግለሰቦች በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ሲያገለግሉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡

ምክር ቤቱ ይኼንን ጉዳይ በተመለከተ የሚነሱ ነገሮችን በግልጽ የማወቅ መብት ስላለው የሁለቱ ባልና ሚስት ማንነት እንዲገለጽ ሲጠይቁ፣ ወ/ሮ አስቴር ማሞ ከእነ ባለቤታቸው፣ እንዲሁም አቶ እውነቱ ብላታ ከእነ ባለቤታቸው መሆናቸውን በግልጽ አስረድተዋል፡፡ ወ/ሮ አስቴር በካናዳ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሲሆኑ፣ ባለቤታቸው እዚያው በዲፕሎማትነት ይሠራሉ፡፡ አቶ እውነቱ እንዲሁ በብራሰልስ በአምባሳደርነት ሲሾሙ፣ ባለቤታቸው እዚያ አብረዋቸው በዲፕሎማትነት እንደሚመሩ ተገልጿል፡፡

‹‹ወ/ሮ አስቴርም ሆኑ ባለቤታቸው በተለያዩ የመንግሥት ተቋማት በፌዴራል ደረጃም ሆነ በክልል ደረጃ (ኦሮሚያ) በተለያዩ ኃላፊነቶች ሲሠሩ የቆዩ ናቸው፡፡ የካበተ ልምድ የነበራቸው መሆኑ በአምሳደርነት ከመመደባቸው በፊት የሚታወቅ ነው፡፡ ነገር ግን ሁለቱም አምባሳደሮች ከእነ ባለቤቶቻቸው አንድ ቦታ መመደባቸውን በተመለከተ ሲነሳ ለነበረው ጥያቄ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በሥልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜም ጭምር ውሳኔ የተሰጠበት ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን አንድ ቦታ መሥራት አለባቸው ብለን አናምንም፡፡ ተገቢም አይደለም፡፡ አሁንም ቢሆን ማስተካከል አለብን፤›› ብለዋል፡፡

ሚኒስትሩ የሁለቱን ሰዎች ጉዳይ በተመለከተ ጥያቄው በሕዝቡም ውስጥ ያለ በመሆኑ ለወደፊቱ ተመሳሳይ ችግሮች ቢኖሩ እንኳ መፍትሔ መኖር ስላለበት፣ በቅርቡ ዕርምጃ በመውሰድ ይስተካከላል በማለት ለምክር ቤቱ ቃል ገብተዋል፡፡

ነገር ግን የሁለቱ ግለሰቦች ምደባ ሲካሄድ የተወሰነው በዝምድና እነሱን ለመጥቀም ታስቦ እንዳልነበር ገልጸው፣ ለወደፊቱ ማንኛውም ሚኒስትር የነበረ ሰው አምባሳደር ሆኖ የሚሾምበት አካሄድ ግልጽ በሆነ አሠራር ቀድሞ በነበረበት ኃላፊነት ያስመዘገበው ልምድና ችሎታ ተገምግሞ እንደሚሆን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

በነዳጅ ማደያዎች የቴሌብር ወኪሎች እንዲነሱ ትዕዛዝ ተላለፈ

በዮናታን ዮሴፍ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሁሉም የነዳጅ ማደያዎች ሲሠሩ የነበሩ የቴሌብርም ሆነ የማደያ ወኪሎች እንዲነሱ ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ለሁሉም የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች፣ ለኢትዮ ቴሌኮምና...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን