Wednesday, March 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበትግራይና በኦሮሚያ ክልሎች ታስረው የነበሩ ከዘጠኝ ሺሕ በላይ ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገላቸው

በትግራይና በኦሮሚያ ክልሎች ታስረው የነበሩ ከዘጠኝ ሺሕ በላይ ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገላቸው

ቀን:

ግድያና ኢሰብዓዊ የወንጀል ተግባር ከፈጸሙ ተከሳሾችና ፍርደኞች በስተቀር፣ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ተከሰውና ፍርድ አርፎባቸው ለነበሩ 9,817 ተከሳሾች የትግራይና ኦሮሚያ ክልሎች መንግሥታት ይቅርታ አደረጉ፡፡

በትግራይ ክልል መንግሥት ይቅርታ የተደረገላቸው 2,206 ታራሚዎች ሲሆኑ፣ 45 ሴቶች መሆናቸውን የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋና የክልሉ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረ መስቀል ታረቀ ተናግረዋል፡፡

ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት በነበሩበት ወቅት በፈጸሙት የወንጀል ድርጊት የተፀፀቱና ሥነ ምግባራቸው የተስተካከለ መሆኑ መረጋገጡን ኃላፊዎቹ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ የኦሮሚያ ክልል ለ7,611 ታራሚዎች ይቅርታ አድርጓል፡፡ ይቅርታ ከተደረገላቸው ውስጥ 7,183ቱ ወንዶች ሲሆኑ፣ 428 ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ አስታውቀዋል፡፡

በክልሉ የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት በርካታ ሥራዎች እንደሚሠሩ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፣ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ክስ ተመሥርቶባቸውና ተፈርዶባቸው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች፣ መታረማቸውና በሠሩት የወንጀል ተግባር መፀፀታቸው እየታየና እየተረጋገጠ ወደ ኅብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግም አስታውቀዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...