Friday, June 9, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከውጭ ከመጣ ደላላ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ የፋይናንስ ኃላፊውን ቢሯቸው ያስጠሩታል]

  • ፈለጉኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • አሁን አንድ ወሳኝ ጉዞ አለኝ፡፡
  • ወደ ፊልድ ሊወጡ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የምን ፊልድ ነው ወደ ውጭ ነው እንጂ?
  • ምን አሉኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ውጭ አገር ልሄድ ነው፡፡
  • የምን ውጭ አገር ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ስማ ዓለም ሁሉ የሚሰበሰብበት ቦታ ላይ ኢትዮጵያን ወክዬ ነው የምገኘው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር አንድ ሚኒስትር እንዴት ነው አገር ወክሎ ውጭ የሚሄደው?
  • ምን ዓይነት ንቀት ነው ያለብህ?
  • ኧረ እኔ ምንም ንቀት የለብኝም፡፡
  • እኔ ኢትዮጵያን ወክዬ ስንት ዓለም እንደዞርኩ አታውቅም?
  • አይ እኔማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያን ወክለው መጓዝ ያለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ናቸው ብዬ ነው፡፡
  • እኔ እኮ ስለማታውቀው ነገር ለምን እንደምትዘባርቅ ነው የሚገርመኝ፡፡
  • ይቅርታ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ካላወቅክ ደግሞ መጠየቅ ይሻላል፡፡
  • ለማንኛውም ክቡር ሚኒስትር ወድጄ አይደለም እንደዚህ የምሆነው፡፡
  • የማዝህን ነገር ብቻ ለምን አትፈጽምም?
  • ቢያዙኝም እኔንም ያስጠይቀኛል፡፡
  • ማን ነው የሚጠይቅህ?
  • መመርያ የወጣበት ጉዳይ እኮ ነው፡፡
  • ስማ እኔ ሳዝህ አትሰማም ማለት ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር ስለሚያስጠይቀኝ እኮ ነው?
  • ስለምን መመርያ ነው የምታወራው?
  • ውጭ አገር ዝም ብሎ መሄድ አይቻልም፡፡
  • ታዲያ እየጮህኩ ልሂድ?
  • ጉዞ ለአገሪቷ አስፈላጊነቱ በሚገባ መጣራት አለበት፡፡
  • ለአገሪቷማ በጣም አስፈላጊ ጉዞ ነው ስልህ?
  • ስለዚህ ከበላይ ትዕዛዝ ሊመጣልኝ ይገባል፡፡
  • የምን ትዕዛዝ?
  • ለእርስዎ አበል በዶላር እንድሰጥ ትዕዛዝ ሊሰጠኝ ይገባል፡፡
  • በቃ አንተም በእኔ ላይ አለቃ እየሆንክ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ እዚህ ያለሁት ላስፈጽም ነው፡፡
  • ምኑን?
  • መመርያውን!

[ክቡር ሚኒስትር ሌላ ሚኒስትር ጋ ይደውላሉ]

  • እንዴት ነው አገሪቷን እየመራን ያለነው?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እኛን እየተበቀላችሁን ነው እንዴ?
  • የምን በቀል ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ስንቱን አይደል እንዴ እየፈታችሁ ያላችሁት?
  • ጥሩ አይደል እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • ታዲያ እኛን ግን የቁም እስረኛ አደረጋችሁን፡፡
  • ምን ሆነው ነው ክቡር ሚኒስትር? ተረጋግተው ያስረዱኝ እስቲ?
  • ሰሞኑን አንድ ወሳኝ የሆነ የውጭ ጉዞ አለብኝ፡፡
  • ምን ዓይነት ጉዞ?
  • በቃ አገሪቷን በመላው ዓለም የሚያስተዋውቅ መድረክ ነው፡፡
  • ይኼማ ጥሩ ነው፡፡ ካቢኔ ላይ ያቅርቡትና ይወሰንበታ?
  • ይኼ ቢሮክራሲ እኮ ነው ያሰለቸኝ፡፡
  • የምን ቢሮክራሲ?
  • እኔ እንደ ሚኒስትርነቴ በዚህ ጉዞ ላይ እንኳን መወሰን አልችልም?
  • ክቡር ሚኒስትር ያኔ መመርያው ሲወጣ ዝም ብለው አሁን እንደዚህ የሚሆኑት ለምንድነው?
  • ለአንድ የውጭ ጉዞ መወሰን የማልችል ከሆነ ብለቅ ይሻለኛል፡፡
  • ምኑን ነው የሚለቁት?
  • ሚኒስትርነቱን፡፡
  • እሱማ ግልግል ነበር፡፡
  • እኔ እንኳን ልብህን ልየው ብዬ ነው እንጂ መቼም አለቅም፡፡
  • የት ለመጓዝ ነው ግን ይኼ ሁሉ ግርግር?
  • ዓለም የተሰበሰበበትና ኢትዮጵያን ላሳይ የምችልበት ቦታ ነው፡፡
  • እኮ የት ነው?
  • የዓለም ዋንጫ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ፊታቸው ላይ በጣም የድካም ገጽታ ይታያል፡፡ ቢሯቸው ውስጥ ከአማካሪያቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ፊትዎ ላይ በጣም የድካም ስሜት ይነበባል፡፡
  • ትናንትና እንቅልፍ አልተኛሁም ነበር፡፡
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የድሮ የአርሴናል ጨዋታዎችን በቲቪ ሳይ ነበር፡፡
  • ምን ተገኝቶ ክቡር ሚኒስትር?
  • አይ አሠልጣኙ ባለራዕይ ስለሆነ ታሪኩ ስለሚመስጠኝ ነው፡፡
  • ለነገሩ ጥሩ አሠልጣኝ ነበር፡፡
  • የሚገርምህ ምንም የማይታወቁ ተጫዋቾችን በዓለማችን ታዋቂ አድርጓቸዋል፡፡
  • ግን ለክለቡ ውድቀትም ተጠያቂ ነው ይባላል፡፡
  • እንዴት ማለት?
  • ማለት አርሴናል በፊት ከነበረው ዝናና አቋም አሁን ወርዷል፡፡
  • የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ሁልጊዜ ልማታዊ ስትሆን በየመንገዱ የተለያዩ እንቅፋቶች ሊገጥሙህ ይችላሉ፡፡
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ቬንገር ልማታዊ አሠልጣኝ ነው፡፡
  • ቡድኑን ለዚህ ውድቀት የዳረጉት ቬንገር ናቸው የሚሉም አሉ እኮ?
  • እነሱ አፍራሽ ኃይሎች ናቸው፡፡
  • ሰውዬው ጡረታ መውጣት በነበረባቸው ጊዜ አልወጣም ብለው ነበር፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ጓደኛቸው አሌክስ ፈርጉሰን በቃኝ ብለው ሲወጡ፣ ይኸው እሳቸው የሙጥኝ ብለው ነበር፡፡
  • እንደ እሱ ዓይነት የኳስ መሐንዲስ ጡረታ አልወጣም ቢል ምን ችግር አለው?
  • ለነገሩ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ያስቸገረው ብዙ ቬንገሮች በመኖራቸው ነው፡፡
  • እንዴት?
  • ይኸው ብዙዎች ሥልጣን ላይ ለ20 ዓመታት የሙጥኝ ብለው አለቅም ብለዋል፡፡
  • በአሽሙር እኔን ለመናገር ፈልገህ ነው?
  • ይቅርታ አድርጉልኝና እርስዎም አንደኛው ቬንገር ነዎት፡፡
  • እ…
  • ይኸው ዴስክዎ ላይ እያንቀላፉ ለወጣቱ ሥልጣኑን ማሳለፍ አይፈልጉም፡፡
  • ምን?
  • ያደለውማ እንደ ቬንገር ሳይሆን እንደ ዚዳን በአጭር ቆይታው ሦስት ዋንጫ በልቶ ሥልጣኑን ይለቃል፡፡
  • ምን ለማለት ፈልገህ ነው?
  • ጡረታ ቢወጡ ጥሩ ነው፡፡
  • እኔማ ጡረታ መውጣት አልፈልግም፡፡
  • በፍላጎት ካላደረጉት በግዴታም ቢሆን ይወጣሉዋ፡፡
  • ስማ ከመንግሥት ፔሮል ብወጣም ከእንትኑ ግን አልወጣም፡፡
  • ከምኑ?
  • ከትግሉ!

[ክቡር ሚኒስትሩ በቅርቡ ከእስር ከተፈታ ባለሀብት ጋር ተገናኙ]

  • እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወዳጄ፡፡
  • አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሰላም ነህ ግን ወዳጄ?
  • ሰውን ማመን ቀብሮ ነው አሉ፡፡
  • ምነው?
  • እንዲያው አንድ ቀን እንኳን መጥተው አይጠይቁኝም?
  • አሁን እኔ ቂሊንጦ አካባቢ ብትይ ምን ሊፈጠር እንደሚችል እያወቅክ?
  • ሌላው ቢቀር እንዴት ቤተሰቤን አይጠይቁም?
  • አገሪቷ በደኅንነት የተሞላች አይደለች እንዴ?
  • ለማንኛውም ግን ቅር ብሎኛል፡፡
  • ምንም ቅር እንዳይልህ፡፡
  • ለምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ለዚህ እንድትበቃ ያልፈነቀልኩት ድንጋይ የለም፡፡
  • ማለት?
  • በየጊዜው ዓቃቤ ሕጎቹንና ዳኞቹን ሳገኝ እንደተሟገትኩልህ ነው፡፡
  • ምን ብለው?
  • ፍጹም ንፁህ መሆንህን ነዋ፡፡
  • እሱን እንኳን ተውት፡፡
  • ስማ አምነስቲ ኢንተርናሽናል በል፣ ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ ብትል፣ ሁሉም ሲያነጋግሩኝ አንተ በፖለቲካ እንደታሰርክ ነበር የምነግራቸው፡፡
  • እኔ እኮ ጋዜጠኛ አይደለሁም፡፡
  • ያው ነው ኤንጂኦ ኤንጂኦ ነው፡፡
  • እና ከጎንህ ነበርኩ እያሉኝ ነው?
  • ይኼንን ማንንም መጠየቅ ትችላለህ?
  • ለማንኛውም ላደረጉልኝ ነገር በጣም አመሰግናለሁ፡፡
  • አንተም ግን ከእስር ቤት የወጣህ አትመስልም፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • በጣም ነዋ ያማረብህ፡፡
  • እሱን እንኳን ተውት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እስር ቤት ራሱ ጥሩ ቦታ እንዲያስሩህ ለኃላፊዎቹ በተደጋጋሚ አስረድቻቸዋለሁ፡፡
  • አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ እኮ አመጣጤም ላደረኩልህ ነገር ትክሰኛለህ ብዬ ነው፡፡
  • ምን ችግር አለው ክቡር ሚኒስትር?
  • ኧረ እባክህ?
  • በደስታ ነው እርስዎን የምክስዎት፡፡
  • ምን ልታደርግልኝ?
  • የምሰጥዎትን እኔ ነኝ የማውቀው፡፡
  • ምንድነው የምትሰጠኝ?
  • የነዳጅ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከውጭ ከመጣ ደላላ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር መንግሥት እያደረገው ያለው ለውጥ በጣም ያስደስታል፡፡
  • ማለት?
  • አገሪቷ ላይ እየነፈሰ ያለው የተስፋ ንፋስ ያስደስታል፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • እስረኞች እየተለቀቁ ነው፣ ፖለቲከኞች እየተፈቱ ነው፡፡ በዚህ ላይ ከመንግሥት ጋር የሚቃረኑ ፓርቲዎች ራሳቸው ጥሪ እየተደረገላቸው ነው፡፡
  • ከዚህ በኋላ እኛ ሰላምና ልማት ላይ ብቻ ነው የምናተኩረው፡፡
  • እኔም አገሬ የገባሁት ይህንን ተረድቼ ነው፡፡
  • ለመሆኑ ምንድነው የምትሠራው?
  • እኔ ፈረንጆቹ አገር የታወቅኩኝ ደላላ ነኝ፡፡
  • ኒዮሊብራል ነህ ማለት ነው?
  • እኔ አገር ወዳድ ሰው ነኝ፡፡
  • ለምንድነው የመጣሁት አልከኝ?
  • መጀመርያ ራሴን ለማሳደግ፣ ቀጥሎ ደግሞ አገሬን ለማሳደግ ነው፡፡
  • እሱስ ጥሩ ሐሳብ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከእርስዎ ጋር ብዙ ሥራ መሥራት እፈልጋለሁ፡፡
  • ምን ዓይነት ሥራ?
  • እኔ ብዙ ኢንቨስተሮች ማምጣት እችላለሁ፣ እርስዎ ደግሞ እዚህ መሬቱንም ሆነ ሌላውን ማመቻቸት ይችላሉ፡፡
  • እኔ ምን እጠቀማለሁ?
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር በኮሚሽን እንጠቃቀማለን፡፡
  • ችግሩ እኮ አንተ ኒዮሊብራል መሆንህ ነው፡፡
  • ለምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ኒዮሊብራል ሳይ ሰውነቴን ይወረዋል፡፡
  • እኔም እኮ አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባለውን ነገር ሳስበው ሰውነቴን ይወረዋል፡፡
  • ምን እያልከኝ ነው?
  • እርስዎም አብዮታዊ ዴሞክራት እንደሆኑ፣ እኔም ኒዮሊብራል እንደሆንኩኝ መቀጠል እንችላለን፡፡
  • ለነገሩ አሁን በምትለው መንገድ መሥራት የምንችልበት ዕድል አለ፡፡
  • እንዴት?
  • ያው መንግሥታችንም አቅጣጫ አስቀምጦልናላ፡፡
  • የምን አቅጣጫ?
  • ከእኛ ጋር ከሚቃረኑ ፖለቲከኞች ጋር አብረን እንድንሠራ አቅጣጫ ስለሰጠን በዚያ መንገድ ማስኬድ እንችላለን፡፡
  • ምን እያሉኝ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እኔና አንተም በዚህ መንገድ ነው የምንሠራው፡፡
  • በምን?
  • በጥምረት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ሒጂራ ባንክ የ143 ሚሊዮን ብር ኪሳራ አስመዘገበ

በኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ ባንክ አገልግሎት ለመስጠት ወደ...

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

ሲሚንቶ በዲጂታል መንገድ ለማገበያየት የክፍያ አማራጮች ልየታ ተጀመረ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሲሚንቶ ግብይትን በዲጂታል መንገድ ለማከናወን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ወልቃይትን ማዕከል ያደረገው የምዕራባዊያን ጫና

በትግራይ ክልል የተከሰተው የዕርዳታ እህል ዘረፋ የዓለም አቀፍ ተቋማት...

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አመሻሹን መኖሪያ ቤታቸው ሲደርሱ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈው የማዕከላዊ ኮሚቴ ገለጻ እየተከታተሉ አገኟቸውና አጠገባቸው ተቀምጠው የደረሱበትን አብረው መከታተል እንደጀመሩ፣ ባለቤታቸው ቴሌቪዥኑን ትተው መጠየቅ...

እኔ ምለው? እሺ... አንቺ የምትይው? የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አባላት እንዲያወሩ ወይም እንዲጠይቁ አይፈቀድም እንዴ? እንዴት ይከለከላል? ታዲያ ለምንድነው ፕሬዚዳንቱ ብቻ የሚያወሩት? እያወሩ አይደለም፣ ገለጻ እያደረጉ ነው። ቢሆንም አንድም አባል...

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...