Monday, September 25, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትር

[ክቡር ሚኒስትሩ አማካሪያቸውን አስጠሩት]

  • ምን አዲስ ነገር አለ?
  • ሪፖርቱ ነዋ፡፡
  • የትኛው ሪፖርት?
  • ሰሞኑን የወጣው፡፡
  • በምን ላይ?
  • በሕገወጥ ዝውውር፡፡
  • የሕገወጥ ዶላሩን ነው?
  • እ…
  • ለእነዚህ ኒዮሊብራሎች ግን የት እንሂድላቸው?
  • ምን እያሉ ነው?
  • ዶላር ከአገር ሸሸ ነው የሚሉት?
  • ኧረ እኔ ሕገወጥ የሰው ዝውውሩን ነው የምልዎት፡፡
  • እእእ…
  • ምነው ደነገጡ?
  • የምን ሕገወጥ ዝውውር ነው?
  • በአፍሪካ ቀንድ የሚደረገው ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ነዋ፡፡
  • ሰዎች እንዳይንቀሳቀሱ ተባለ እንዴ?
  • በዚህ ወንጀል ላይ ባለሥልጣናትም ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
  • እኛ?
  • አይ የለም የኤርትራ ባለሥልጣናትን ነው፤ ምነው ደነገጡ?
  • እኔን ያልከኝ መስሎኝ ነዋ?
  • እርስዎማ በዚህኛው ዝውውር መቼ ይጠረጠራሉ?
  • በየትኛው ዝውውር ነው የምጠረጠረው?
  • እ…
  • ለመሆኑ ምንድን ነው ባለሥልጣናቱ የሚያደርጉት?
  • ሰዎች በሕገወጥ መንገድ ከአገራቸው እንዲፈልሱ ያደርጋሉ፡፡
  • እኮ ለምን?
  • ዶላር ለማግኘት ነዋ፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • በቃ ከሰዎቹ ዶላር ይቀበላሉ፡፡
  • ዕቃ ኤክስፖርት ማድረግ ሲያቅታቸው ሰው ኤክስፖርት ማድረግ ጀመሩ ማለት ነው?
  • እንደዚያ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ዘዴኛዎች ናቸው ባክህ፡፡
  • እንዴት?
  • ያው በተዘዋዋሪም ቢሆን እያገኙት ነዋ፡፡
  • ምኑን?
  • ዶላሩን፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ይህ እኮ ከፍተኛ ወንጀል ነው፡፡
  • ማነው ያለው?
  • የሰዎች ዝውውር እኮ ነው፡፡
  • ቢሆንስ?
  • ምን ነካዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ይኼ የኒዮሊብራሎች ትምክህት ነው፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • እነሱ በገንዘብ ሰው ያዘዋውራሉ አይደል እንዴ?
  • መቼ ነው ያዘዋወሩት?
  • ይኼው እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ከአንድ ክለብ ወደ ሌላው ክለብ በከፍተኛ ገንዘብ አይደል እንዴ የሚዘዋወሩት?
  • እሱ እኮ ሕጋዊ ነው፡፡
  • ይኼኛውስ?
  • ሕገወጥ ነዋ፡፡
  • ለምን እኛ አንሞክረውም ግን?
  • ምኑን? ዝውውሩን?
  • ሕጋዊ ዝውውሩን፡፡
  • በኳስ ተጨዋቾቻችን?
  • በእነሱ ሳይሆን በአትሌቶቻችን፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር አያውቁም እንዴ?
  • ምኑን?
  • በአትሌት ስም ስንቱ በርካታ ገንዘብ እየከፈለ ከአገር እንደሚወጣ፡፡
  • ምን?
  • ትንሽ ዘገዩ፡፡
  • ለምኑ?
  • ለዚህኛው ቢዝነስ፡፡
  • እንዴት?
  • በሌሎች ተቀድመዋል፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ ቦታ ከሾፌራቸው ጋር እየሄዱ ነው]

  • እዚህ ጋ አቁም!
  • ኧረ አይቻልም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምንድነው የማይቻለው?
  • የተከለከለ ቦታ ነው፡፡
  • ማን ነው የከለከለው? አቁም!
  • ኧረ የእንጀራ ገመዴን ያስበጥሱብኛል፡፡
  • ከእኔ ውጪ ማን ነው የአንተን የእንጀራ ገመድ የሚበጥሰው?
  • አዲስ ሕግ ወጥቷል፡፡
  • ምን የሚል?
  • ተደጋጋሚ ጥፋት ያጠፋ ይቀማል የሚል፡፡
  • ምኑን ነው የሚቀማው?
  • መንጃ ፈቃዱን?
  • መፍጃ ፈቃዱን ነው ያልከኝ?
  • በሉት፡፡
  • በል አሁን አቁም፡፡
  • ኧረ ይኼ ሦስተኛ ቅጣቴ ነው የሚሆነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ሕጉን ያወጣነው እኛው አይደለን እንዴ?
  • የሚተገበረው እኛ ላይ ነዋ፡፡
  • እንዲያውም ትራፊኩ ያውና ንገረውና አቁመው፡፡

[የክቡር ሚኒስትሩ ሾፌር ትራፊኩን ክላክስ አድርጐ ጠራው]

  • እዚህ ጋ ላቁም?
  • አዲስ የወጣውን ሕግ ታውቃለህ አይደል?
  • በሚገባ፡፡
  • እዚህ ጋ ላቁም ብለህ በማሰብህ ራሱ ልቀጣህ እችላለሁ፡፡
  • ይቅርታ እንግዳ ስለያዝኩ ነው፡፡
  • አይደለም እንግዳ ለምን ባለሥልጣን አትይዝም?
  • ምን አልከኝ?
  • የእንጀራ ገመድህን እንዳልበጥስልህ፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ ከኋላ የመኪና መስታወታቸውን አወረዱት]

  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • እዚህ ጋ አንድ ቀጠሮ ነበረኝ፡፡
  • ምን ላድርግልዎት ታዲያ ክቡር ሚኒስትር?
  • እዚህ ጋ ብናቆም ብዬ ነው፡፡
  • አይደለም ማቆም አዝለህ ውሰደኝ ቢሉኝ አልወስድዎትም እንዴ?
  • እንዲህ ነው እንጂ፡፡
  • ሊጋልቡኝ ይችላሉ ስልዎት፡፡
  • እሱን ሌላ ጊዜ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔም እፈልግዎት ነበር፡፡
  • ቢሮ ና፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሾፌራቸው ጋ ወሬያቸውን ቀጠሉ]

  • እኔ እኮ አይገባኝም፡፡
  • ምኑ ክቡር ሚኒስትር?
  • የመልካም አስተዳደር ችግር አለ የሚባለው፡፡
  • እንዴት?
  • ከዚህ በላይ መልካም አስተዳደር አለ? 
  • መልካም አስተዳደር ያለው እኮ ለእኛ አይደለም፡፡
  • ለማን ነው ያለው ታዲያ? 
  • ለእናንተ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከቀጠሯቸው የውጭ ዜጐች ጋር ተገናኙ]

  • ክቡር ሚኒስትር እዚህ አገር ብዙ ሥራ መሥራት እንፈልጋለን፡፡
  • የሚሠራን ሰው እናበረታታለን፡፡
  • አገራችሁን እንደ አገራችን ለማሳደግ ቆርጠን ተነስተናል፡፡
  • አገራችሁ አድጋለች እንዴ?
  • ለዓለም ሁሉ ዕቃ የምናቀርበው እኛ አይደለን እንዴ?
  • ለነገሩ እውነታችሁን ነው፡፡
  • እዚህ አብዮት ማስነሳት ነው የምንፈልገው፡፡
  • ኒዮሊብራሎች ናችሁ እንዴ? የምን አብዮት ነው?
  • የለም የለም፤ የገበያ አብዮት ነው የምልዎት፡፡
  • እሱኛውን አብዮት ማስነሳት ትችላላችሁ፡፡
  • አገሪቷን እናስመነድጋታለን ስልዎት፡፡
  • ለልማት በራችን ክፍት ነው፡፡
  • አንዳንድ ነገሮች ግን አስቸግረውናል፡፡
  • ምን ዓይነት አንዳንድ ነገሮች?
  • ቀረጥና ፈቃድ ማውጣት የመሳሰሉት፡፡
  • ያስቸገሯችሁ ከሌላ ጋር እየሠራችሁ በመሆኑ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እርስዎ ወሳኝ መሆንዎት ገብቶን እኮ አሁን ወደ እርስዎ የመጣነው?
  • ቢሆንም ዘግይታችኋል፡፡
  • አንዳንድ ኪራይ ሰብሳቢዎች አሳስተውን ነው፡፡
  • ለማንኛውም እነዚህን ነገሮች እኔ እጨርሳቸዋለሀ፡፡
  • ምን እናድርግ ታዲያ?
  • በአስቸኳይ እንፈራረማ፡፡
  • ስለእሱ አያስቡ፤ አሁኑኑ ድርጅቱን እንመሠርታለን፡፡
  • እኔም ሌላውን እጨርሳለሁ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር…
  • አቤት፡፡
  • ልንሠራው ያሰብነው ቢዝነስ ግን ለኢትዮጵያውያን ብቻ የተፈቀደ ነው፡፡
  • ታዲያ ምን ችግር አለው?
  • እኛ የውጭ አገር ዜጐች ነና፡፡
  • ኢትዮጵያውያን ትሆናላችኋ፡፡
  • እንዴት?
  • በእኔ በኩል!

[ክቡር ሚኒስትሩ ቢሯቸው ቁጭ ብለው በሞባይላቸው ካንዲ ክራሽ የሚባለውን ጌም ሲጫወቱ ጸሐፊያቸው ገባች]

  • ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ፈለግሽ?
  • እንግዳ ይፈልግዎታል፡፡
  • ሥራ ይዟል በይ፡፡
  • ኧረ ስድስት ወር ሙሉ ሲመላለስ ነበር፡፡
  • በቃ ሌላ ስድስት ወር ይጠብቃ፡፡
  • ምን እየሠሩ ነው ግን?
  • ከባድ ሥራ ይዣለሁ፡፡
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር ካንዲ ክራሽ እየተጫወቱ ነው እንዴ?
  • ትጫወቻለሽ እንዴ አንቺም?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት አዕምሮ የሚያሠራ ጌም መሰለሽ?
  • አውቃለሁ ስንተኛው ሌቭል ላይ ነዎት?
  • 100 ደርሻለሁ፡፡
  • እርስዎና ኢሕአዴግ ግን ይኼን ቁጥር ትወዱታላችሁ፡፡
  • የቱን ቁጥር?
  • 100!

[ክቡር ሚኒስትሩ የጌሙን ሌቭል ማለፍ አቅቷቸው ተክዘው ቁጭ ብለው ሚስታቸው መጡ]

  • ምን ሆነህ ነው የተከዝከው?
  • ኧረ ተይኝ እባክሽ፡፡
  • ምን ሆንክ?
  • ማደግ አቃተኝ እኮ፡፡
  • ያቺ 11 ፐርሰንቷ ቀረች እንዴ?
  • እሷማ እንደቀጠለች ነው፡፡
  • የሥራ ዕድገት ጠየቅክ እንዴ ታዲያ?
  • ሕይወት ተቀጥፎብኝ ነው፡፡
  • ምን ሆነሃል ሰውዬ? ሁላችንም ሰላም ነን እኮ፡፡
  • አይ እኔ መቼ የእናንተ ሕይወት አሳሰበኝ?
  • የማን ሕይወት ነው ያሳሰበህ ታዲያ?
  • የጌሙ ነዋ፡፡
  • የምን ጌም?
  • ምን ይቺ ልጅሽ ጊዜ ሲኖርህ ተጫወተው ብላ አንድ ጌም አሳይታኝ ይኸው ሱስ ይዞኝ አርፏል፡፡
  • ጌም ነው ያልከኝ?
  • አዎን፡፡
  • ሥራውን ትተህ ጌም?
  • እንዴት ጭንቅላት የሚጠይቅ ጌም መሰለሽ?
  • ምን የሚሉት ጌም ነው?
  • ካንዲ ክራሽ፡፡
  • በል ተጠንቀቅ፡፡
  • ምኑን?
  • አንተ ካንዲ ክራሽ ስታደርግ …
  • እ…
  • አንተ ራስህ ክራሽ እንዳትደረግ፡፡
  • በማን?
  • በሕዝቡ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

በቀይ ባህር ፖለቲካ ላይ በመከረው የመጀመሪያ ጉባዔ ለዲፕሎማቲክና ለትብብር አማራጮች ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ ቀረበ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ለመጀመርያ ጊዜ በቀይ ባህር ቀጣና የፀጥታ...

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...

የመጀመርያ ምዕራፉ የተጠናቀቀው አዲስ አበባ ስታዲየም የሳር ተከላው እንደገና ሊከናወን መሆኑ ተሰማ

እስካሁን የሳር ተከላውን ጨምሮ 43 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል ዕድሳቱ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...

[የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ ክቡር ሚኒስትር ሌሊቱን በእንቅልፍ ልባቸው በህልም እየተወራጩ ሳለ የሞባይል ስልካቸው ጥሪ አነቃቸው። አለቃቸው ስለነበሩ ስልኩን በፍጥነት አነሱት]

በሌሊት ስለደወልኩኝ ይቅርታ፡፡ ችግር የለውም ክቡር ሚኒስትር፣ ምን ልታዘዝ? አንድ የአውሮፓ ባለሥልጣን ነገ በጠዋት ወደ አዲስ አበባ ይገባል። እሺ። ሌሎች የመንግሥት አመራሮች ስላልቻሉ እርስዎ መንግሥትን ወክለው ቦሌ ኤርፖርት...