- Advertisement -

መኢአድ የአልጀርሱን ስምምነት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል የአገር ክህደት ነው አለ

ባለፈው ሳምንት መጀመርያ ላይ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የአልጀርስን ስምምነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደሚቀበል መግለጹ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አስታወቀ፡፡

መኢአድ ይህን ያስታወቀው ማክሰኞ ሰኔ 5 ቀን 210 ዓ.ም. ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤቱ ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ጋዜጠኞች፣ ‹‹አሳሪ የሆነውን የአልጀርሱን ስምምነት ያለኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ተቀብያለሁ ማለት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው፤›› በማለት በሰጠው መግለጫ ነው፡፡

መኢአድ በመግለጫው እንዳስታወቀው የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባለፈው ሳምንት የወሰነው ውሳኔ፣ ሦስተኛው የአገር ክህደት ነው ብሎታል፡፡ ‹‹ከ27 ዓመታት በፊት ያለ ሕዝብ ፍላጎት አገራችንን ባህር አልባ ማድረጉ የመጀመርያው የአገር ክህደት ነው፡፡ የአልጀርሱን ስምምነት ፈርሞ በስምምነቱ ወቅት አሰብን ማስመለስ ሲቻል፣ ጭራሹን ተጨማሪ ቦታ ከኢትዮጵያ ለኤርትራ እንዲሰጥ መወሰኑ ሁለተኛው ክህደት ነው፤›› በማለት ገልጿል፡፡

‹‹ለ20 ዓመታት ገዥው ፓርቲ የተለያዩ ምክንያት በመስጠት የድንበር ኮሚሽኑ የወሰነውን ውሳኔ ሳይተገብር ቢቆይም፣ ሰሞኑን የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሕዝብን ፈርቶ ተግባራዊ ለማድረግ ያልደፈረውን ፀረ ኢትዮጵያ ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑ ሌላ ሦስተኛ የአገር ክህደት ነው፤›› በማለት ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡

በመሆኑም መኢአድ በአልጀርሱ ስምምነት መሠረት የተቋቋመውን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ መቀበል አንደኛ የአገር ክህደት ከመሆን ባለፈ፣ በምንም መሥፈርት በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ቀውስ የሚፈታ ሳይሆን እንዲያውም የሚያባብስ ነው ብሏል፡፡  ኢትዮጵያን መጀመርያ የወረረው የኤርትራ መንግሥት ሆኖ እያለ፣ የሻዕቢያን ፍላጎት ማሟላትና ለሻዕቢያ ባድመን መሸለም ወረራና ጥፋትን ማበረታታት ነው ብሎ እንደሚያምን ፓርቲው አስታውቋል፡፡

‹‹በአጠቃላይ ይህንን አሳሳቢ የሆነ ጉዳይ ኢሕአዴግ ብቻውን የመወሰን ሥልጣን ስለሌለው፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ያገባኛል ከሚሉ ድርጅቶች ጋር በመነጋገር አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠው እንጠይቃለን፤›› በማለት መኢአድ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

- Advertisement -

‹‹በአልጀርሱ ስምምነት የቀረቡት ጭብጦች የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዱ በመሆናቸው እንደገና ሊጤኑ እንደሚገባ፣ የድንበር ኮሚሽኑ ውሳኔ በአካባቢው የሚኖሩትን ማኅበረሰቦች ማንነት አደጋ ውስጥ የሚጥልና ለሁለት ሊከፈሉ የማይችሉ የእምነት ተቋማትን፣ የመቃብር ሥፍራዎችን፣ መኖርያ ቤቶችን፣ ትምህርት ቤቶችን ለሁለት የሚከፍልና ቤተሰብንና ዘመድ አዝማድን የሚበትን ነው፤›› በማለት ውሳኔውን አጥብቆ እንደሚቃወም ፓርቲው አስታውቋል፡፡

ምንም እንኳን ገዥው ፓርቲ እውነቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በመደበቅ ባድመን ጨምሮ አወዛጋቢ አካባቢዎች ለኢትዮጵያ እንደተሰጡ ቢገልጽም፣ የድንበር ኮሚሽኑ ውሳኔ ግን ባድመን ጨምሮ በርካታ የኢትዮጵያ ግዛቶችን ሙሉ ለሙሉ ለኤርትራ የሰጠ፣ የኢትዮጵያን ጥቅም የደፈረ በወቅቱ በነበረው ጦርነት ደማቸውን ያፈሰሱ ከመቶ ሺሕ በላይ ዜጎችን መስዋዕት ያረከሰ ውሳኔ በመሆኑ ተቀባይነት እንደሌለው መኢአድ አስታውቋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የኢትዮጵያ ጂዲፒ በውጭ ምንዛሪ ለውጡ ምክንያት ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር መውረዱ ተገለጸ

የአገሪቱ የውጭ ዕዳ ጂዲፒ ጥምርታ ለደሃ አገሮች ከተቀመጠው ጣሪያ አልፏል የኢትዮጵያ ኖሚናል ጂዲፒ (የዋጋ ንረትን ታሳቢ ያላደረገ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት) በዶላር ሲተመን፣ በሰኔ ወር...

ከአፋር በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለተፈናቀሉ ተጨማሪ ድጋፍ ተጠየቀ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች በሙሉ ተፈናቅለዋል ተብሏል በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን በሚገኙት በአዋሽ ፈንታሌና በዱለቻ ወረዳዎች በቀጠለው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች እየቀረበ ያለው...

በውዝግብ የተሞላው 18ኛው የአዲስ አበባ የንግድ ዘርፍ ማኅበራት ጉባዔና ምርጫ እያነጋገረ ነው

ከጉባዔው አንድ ቀን በፊት አባል ሆነው የተመረጡ 55 ነጋዴዎች ለቦርድ አባልነት መቅረባቸውም ግርምትን ፈጥሯል የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት መተዳደሪያ ደንብ፣ ጠቅላላ ጉባዔው...

የአየር ንብረት ለውጥ በግብርናው ዘርፍና አመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጫና በኢትዮጵያ ግብርናና የአመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ፡፡ ይህ የተነገረው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብና...

በምርጫ ወቅት ማጭበርበር አምስት ዓመታት እንደሚያስቀጣ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን ለመተካት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተረቀቀው አዲስ አዋጅ፣ በተጭበረበረ መረጃ ለመወዳደርና ለመመረጥ የሚሞክሩ...

በመጀመሪያው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ መቸገራቸው በጥናት ተረጋገጠ

በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 75 በመቶ ተጠቃሚዎች የመኪና ማቆሚያ ቦታ ለማግኘት መቸገራቸው በጥናት መረጋገጡን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮና ሁለት የግል ተቋማት አስታወቁ፡፡ ጥናቱ የቀረበው ጥር...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን