Sunday, October 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ የሴቶች የዓለም ዋንጫን ለመዳኘት ታጨች

ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ የሴቶች የዓለም ዋንጫን ለመዳኘት ታጨች

ቀን:

በካዳና በሚዘጋጀው የሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ ለመዳኘት ኢትዮጵያዊቷ ኢንተርናሽናል ዳኛ ሊዲያ ታፈሰ ታጨች፡፡ 22 ዋና ዳኛዎች ሰባት ዕረዳት ዳኞችና 44 ምክትል ዳኞች ከተለያዩ የዓለም አገሮች መመረጣቸውን የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር ፊፋ በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡

በዚህ 24 አገሮች በሚሳተፉበት የሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ ዳኞች የተመረጡት የዳኝነትን የጨዋታ አግባብ በመረዳት፣ የግል ችሎታቸውን በመመልከትና በጨዋታዎች ላይ የሚያደርጉት እንቅስቃሴን ባገናዘበ መልኩ እንደሆነም ዘገባው አመልክቷል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛምብያ፣ ካሜሮን፣ ቶጎ፣ ማላዊ፣ ሞሮኮና ማዳጋስካር ለዚህ ጨዋታ ዳኞችን ካስመረጡት ይገኙበታል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም የተመረጡት ዳኞች እ.ኤ.አ. ሚያዝያ ወር ላይ ውድድሩ ከመጀመሩ ቀደም ብሎ ሁለት የዳኝነት ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር ፊፋ በበኩሉ ለተመረጡት ሴት ዳኞች ከፍተኛ ድጋፍ ለማድረግ እንደተዘጋጀም ገልጿል፡፡  በውድድሩ ለመጀመርያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ እንደሚገጠምለት ለሚጠበቀው የዘንድሮው የሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ከአፍሪካ ኮትዲቯር፣ ካሜሮንና ናይጄሪያ ተካፋይ ይሆናሉ፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...