በብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹ ሲመራ የነበረው የኦሮሞ አንድነትና ነጻነት ግንባር (ኦአነግ) የትጥቅ ትግል ትቶ ወደ አገር ውስጥ ገባ፡፡
ዘጠኝ አባላት ያሉት አዲስ አበባ የገባው የልዑካን ቡድን በአቶ ተማም ባቲ የተመራ ሲሆን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን (ዶ/ር) ጥሪ ተቀብለው እንደመጡና ፓርቲ አቋቁመው ለመንቀሳቀስ እንደሚያስቡ ተናግረዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ አባላት በአሜሪካ፣ በአውሮፓና በካናዳ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ፡፡
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ የልዑካን ቡድኑ አባላትን በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተቀብለዋቸዋል፡፡