Saturday, September 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከፓርቲ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከፓርቲ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ

ቀን:

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባደረገው ስብሰባ፣ የድርጅቱ ሊቀመንበር በመሆን ከየካቲት 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፡፡

አቶ ሽፈራው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርና የደኢሕዴን ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን ተክተው ነበር ወደ ሊቀመንበርነት የመጡት፡፡

አቶ ሽፈራው በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተዋቀረው አዲሱ ካቢኔ የግብርናና የእንስሳት ሀብት ልማት ሚኒስትር ሆነው መሾማቸው ይታወሳል፡፡

በቅርቡ በደቡብ ክልል በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶና በወልቂጤ ከተሞች በተከሰቱ ግጭቶች በርካቶች በመሞታቸውና በመፈናቀላቸው ምክንያት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልሉ በተዋረድ ያሉ ባለሥልጣናት ከሥልጣናቸው በገዛ ፈቃዳቸው እንዲሰናበቱ ማሳሰባቸው ይታወሳል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...