Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበሕገወጥ መንገድ 98 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ሰብረው የያዙ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

በሕገወጥ መንገድ 98 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ሰብረው የያዙ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

ቀን:

እየተካሄደ ባለው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ቆጠራ 98 ቤቶች በሕገወጥ መንገድ የተያዙ መሆናቸው በመረጋገጡ፣ በሕገወጥነት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡

እስከ ዓርብ መጋቢት 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ 94,101 ቤቶች መቆጠራቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ቆጠራው መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡

በሕገወጥ መንገድ የተያዙት ቤቶች በአብዛኛው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚገኙ ናቸው፡፡ ግለሰቦቹ ቤቶቹን ሰብረው በመግባት መኖር የጀመሩ፣ የሚያከራዩ፣ ከራሳቸው ቤት ጋር ቀላቅለው የያዙ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ዋለልኝ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

እነዚህ ሕገወጥ ተግባር የተፈጸመባቸው ቤቶች ለልማት ተነሽዎች ተብለው የተቀመጡ ነበሩ፡፡ ለልማት ተነሽዎች ለመስጠት በሚታሰብበት ወቅት አብዛኛዎቹ የልማት ተነሽዎች ፍላጎት ባለ ሁለትና ባለ ሦስት መኝታዎች በመሆኑና እነዚህ ቤቶች ደግሞ ስቱዲዮና ባለ አንድ መኝታ በመሆናቸው ያለ አገልግሎት ተቀምጠው ነበር፡፡

ቤቶቹ ባዷቸውን በመቀመጣቸው ለሕገወጥ አገልግሎት የዋሉ በመሆኑና አስተዳደሩም ሕግ ማስከበር ስላለበት ዕርምጃ መውሰዱን አቶ ይድነቃቸው ተናግረዋል፡፡

ለልማት ተነሽዎች ተብሎ ባዷቸውን ተቀምጠው ከነበሩ ከስምንት ሺሕ በላይ ቤቶች ውስጥ እስካሁን 1,200 የሚሆኑት በነበሩበት ተገኝተዋል ተብሏል፡፡

ቆጠራው ሙሉ በሙሉ ከተጠናቀቀ በኋላ በሕገወጦቹ ላይ የሚወሰደው ዕርምጃ ይፋ እንደሚሆን አቶ ይድነቃቸው ተናግረዋል፡፡

የኮንዶሚኒየም ቤቶች ከዕጣ ውጪ በሌላ መንገድ ሊተላለፉ ስለማይችሉ እጅግ መጠነ ሰፊ የቤት ችግር ባለባት አዲስ አበባ፣ እነዚህ ቤቶች ያለተጠቃሚ እንዲቆዩ መደረጉን ሪፖርተር ከአስተዳደሩ ያገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...