Friday, June 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅአገሬ እንዴታ!

አገሬ እንዴታ!

ቀን:

በኢትዮጵያ ጥንተ ህልውና

በክብረ ወሰኗም ÷ ሀብተ ብልፅግና

ታፍሮና ተከብሮ ÷ ጥንቱን እንደ ጸና

የሕዝቡ ህሊና፤

ጥርጣሬ የለው ÷ እንበለ ምስጋና 

ላበው ተጋድሎ ÷ መዋዕለ ዜና፡፡

ግና፣

ዓለም ወረተኛ ÷ ፍቅሯም ውስጠ ወይራ

ዓይነ ዓዋጅነቷም ÷ የለው ባለ ጋራ፡፡

ውበት ደም ግባቷ ÷ ወትሮ እየጎላ

ቢያማልል ወንድ ሁላ ÷ ቢያስቀና ሴት አውላ፤

ቀልቡ መች ይዞለት ÷ ፍላጎቱ ይሞላ

‘ሚያነሳ ‘ሚጥለው ÷ ደግሞ ሌላ ሌላ፡፡

የምድሩ ልምላሜ ÷ ያየሩ ጠባይ

ጋራ ሸንተረሩ ÷ መልኩ አማላይ

ወዙም ጥርት ብሎ ÷ ከመ ገጸ ማይ

የሰው ፊት ያሳያል ÷ ለሱስ ባይታይ፡፡

ያቺ የንጋት ጀንበር ÷ ያቺ ብሩህ ፀሐይ

የምትመላለስ ÷ መች ያለ ጉዳይ

ጎሕ ሲቀድ ማለዳ ÷ ወገግ ሲል ሰማይ

የቀኑም አባዜ ÷ የሰዉም ይለይ፡፡

ሠርክ ኾነ ማለዳ ÷ ቀንም ኾነ ማታ

እየተዟዟረ ÷ የጊዜው ኹኔታ

በቀድሞ ይዞታ ÷ በኖረበት ቦታ

ቢሹት የሚያገኙት ÷ አገሬ እንዴታ!

  • ኃይለ ልዑል ካሣ

(ሐምሌ 5 ቀን 2010 ዓ.ም.)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ