Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትበመኪና አደጋ ሕይወቱ ያለፈው አትሌት ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

በመኪና አደጋ ሕይወቱ ያለፈው አትሌት ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

ቀን:

ከአዲስ አበባ በሰበታ ከተማ በኩል 35 ኪሜ ርቀት በምትገኘው አዋሽ ከተማ በጎዳና ሩጫ ልምምድ ላይ ሳሉ በሚኒባስ ተሸከርካሪ ጉዳት ከደረሰባቸው 11 አትሌቶች መካከል ሕይወቱ ያለፈው አትሌት አሻግሬ ግርማ ሥርዓተ ቀብር ተፈፀመ፡፡

መጋቢት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.  ከአዲስ አበባ የተነሱትና ሰበታ ከተማን አልፈው ልምምድ ሲያደርጉ ከነበሩት አትሌቶች አምስቱ ከፍተኛ አደጋ ሲደርስባቸው አራቱ መጠነኛ አደጋ እንደደረሰባቸው ታውቋል፡፡

በሆስፒታል ሕክምና ሲደረግለት የቆየው አትሌት አሻግሬ ያረፈው መጋቢት 19 ቀን ሲሆን፣ ሥርዓተ ቀብሩም መጋቢት 21 ቀን በትውልድ ቦታው አርሲ ሮቤ መፈጸሙን የኢትዮጵያ አትሌቶች ማኅበር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ ገዛኸኝ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ጉዳት የደረሰባቸው አትሌቶችም  ሕክምናቸውን እየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡

 

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...