Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላ ወዳጃቸው ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው

  • ክቡር ሚኒስትር እንዴት ነዎት?
  • ደህና ነኝ፡፡
  • መግለጫውን ሰሙት?
  • የትኛውን መግለጫ?
  • እኛን የሚመለከተውን መግለጫ ነዋ፡፡
  • ኢትዮ ኤርትራ ላይ የተሰጠውን መግለጫ ነው?
  • እሱ እኛን አይመለከትም እኮ፡፡
  • ባለፈው ኤርትራ ሄደን ኢንቨስት እናደርጋለን ስላልከኝ ነዋ፡፡
  • እሱን የሚመለከት ሳይሆን እኛን በዋናነት የሚመለከት መግለጫ ወጥቷል፡፡
  • ምንድነው እሱ?
  • የብሩ ጉዳይ ነዋ፡፡
  • የምን ብር?
  • በካዝና ያስቀመጥነው ብር ጉዳይ ነዋ፡፡
  • ስማ ላባችንን አንጠፍጥፈን ያመጣነው ገንዘብ አይደል እንዴ?
  • ምን አሉኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ጥረን ግረን ባፈራነው ገንዘብ እኮ ልንሸማቀቅ አይገባም፡፡
  • መንግሥት እኮ ይኼ አይገባውም፡፡
  • እንዴ በአገራችሁ አትሥሩ እየተባለ ነው?
  • መንግሥትማ ሕዝቡ ሠርቶና ለፍቶ እንዲያድግ ነው የሚፈልገው፡፡
  • ታዲያ እኛ የሕዝቡ አንድ አካል አይደለንም እንዴ?
  • እሱማ ነን፡፡
  • ታዲያ የራሳችንን ብር ባንክ አስቀመጥነው ካዝናችን ውስጥ አስቀመጥነው መንግሥት ምን አገባው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኛም ካዝና ውስጥ ያስቀመጥነው ለምን እንደሆነ ያውቃሉ መቼም?
  • እኛ እኮ ባንኩን ስለማናምነው ነው ቤታችን በካዝና የምናስቀምጠው፡፡
  • ምክንያታችንማ እሱ አይደለም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምንድን ነው ታዲያ ምክንያታችን?
  • ባንክ ያለንን የገንዘብ መጠን እንዳያውቅብን ነዋ፡፡
  • እሱስ ቢሆን እንደ ሳዑዲ ባለሀብቶች ሀብታችንን የመደበቅ መብት የለንም እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር ሀብቱም እኮ ቢሆን የእኛ አይደለም፡፡
  • ታዲያ የማነው?
  • ያው ግማሹ የስኳር፣ ግማሹ የባቡር ነው፡፡
  • እና አትደልሉ ልንባል ነው?
  • መደለልማ እንችላለን፡፡ እኛ ግን ሕገወጥ ድለላ ነው ያደረግነው፡፡
  • ለማንኛውም እኔ በዚህ አልስማማም፡፡
  • እኔ እኮ መግለጫው አስፈርቶኝ ነው፡፡
  • መግለጫው ምንድነው የሚለው?
  • ቤታችሁ ያለውን ገንዘብ አውጥታችሁ ባንክ አስቀምጡ እየተባልን ነው፡፡
  • ባናስቀምጥስ ምን ሊያደርጉን ነው?
  • ኦፕሬሽን እንጀምራለን ብለዋል፡፡
  • የምን ኦፕሬሽን ነው?
  • ያው እንግዲህ የቤት ለቤት አሰሳ ሊጀምሩ ይሆናላ፡፡
  • ካሰሳው በኋላ ምን ሊያደርጉ?
  • ካገኙማ ይወርሱናል፣ በዚያ ላይ ሌላ መዘዝ ሊኖረው ይችላል፡፡
  • ታዲያ አንተ ምን አሳሰበህ?
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር ከመንግሥት ኦፕሬሽን በፊት ብሩን ባንክ እንዲያስገቡት ነዋ?
  • እኔማ ሰሞኑን ይኼንኑ መግለጫ ሰምቼ ብሩን ወደ ሌላ ቦታ ለማሸሽ አስቤ ነበር፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ብቻ በመንግሥት ኦፕሬሽን ጉድ እንዳይሆኑ፡፡
  • ከመንግሥት ኦፕሬሽ በፊት በሌላ ኦፕሬሽን ጉድ ተሠርቻለሁ፡፡
  • በምን ኦፕሬሽን?
  • በአይጥ ኦፕሬሽን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ምሳ ሊበሉ ቤት ሄደው ከሚስታቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • ሰዓቱ ረፍዷል እኮ ቢሮ አትገባም እንዴ?
  • ባክሽ ዛሬ ቢሮ መግባት አልፈልግም፡፡
  • ምን ሆንክ ደግሞ?
  • ራሴን አሞኛል፡፡
  • ምን ሆነህ?
  • ሰሞኑን ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቻለሁ፡፡
  • ማታም እኮ ምንም እንቅልፍ አልተኛህም ነበር፣ ያው ሥራ ይኖርሃል ብዬ ነው፡፡
  • ምን ሥራ ይኖራል ብለሽ ነው? ብቻ ምንም ሰላም እየተሰማኝ አይደለም፡፡
  • የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ?
  • የሰማሁት ነገር እየረበሸኝ ነው፡፡
  • ልትታሰር ነው እንዴ?
  • ኧረ ከኃላፊነቴ ሊያስነሱኝ ሳያስቡ አልቀረም፡፡
  • እንዴት አወቅክ?
  • መሥሪያ ቤት ሌላ ሰው አምጥተውብኛል፡፡
  • በላይህ ላይ?
  • አዲስ ሚኒስትር ዴኤታ ተሹሞብኝ ነው፡፡
  • ምን ችግር አለው ታዲያ?
  • ሰውየውን ቀልቤ አልወደደወም፣ አስፈርቶኛል፡፡
  • ዝም ብሎ ሰው አስፈራኝ ብሎ ነገር አለ እንዴ?
  • ለነገሩማ ስለሰውየውም እያጣራሁ ነው፡፡
  • ታዲያ ምን አገኘህ?
  • ሰውየው ሁለት ዶክትሬት ዲግሪ ነው ያለው፡፡
  • አንተስ ቢሆን አንድ የዶክትሬት ዲግሪ አለህ አይደል እንዴ?
  • የእኔ ታዲያ በግዥ ነዋ፡፡
  • የሰውየውስ ትክክለኛ መሆኑን አጣርተሃል?
  • እንዲያውም ሁለቱንም በወርቅ ሜዳሊያ ነው የጨረሰው፡፡
  • ምን ትቀልዳለህ? ሌላስ?
  • ስሚ ዩኤን በይው ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያልሠራበት ቦታ የለም፡፡
  • አንተስ ቢሆን ስንትና ስንት የውጭ ድርጅቶችን እያማከርክ አይደል እንዴ ያለኸው?
  • እኔ እኮ የውጭ ድርጅቶቹን የማማክረው በማስፈራራት ነው እንጂ እንደ እሱ በችሎታ አይደለም፡፡
  • እሱ ግን የውጭ ድርጅቶች ውስጥ የሚሠራ ከሆነ ለምን እናንተ ጋ መምጣት ፈለገ?
  • የሚገርምሽ እኮ ደመወዙን በስንትና ስንት ቀንሶ ነው ለመሥራት የመጣው፡፡
  • በጣም ነው የሚገርመው፡፡
  • ይኼ ደግሞ ሰውየው ምንም ለገንዘብ ደንታ እንደሌለው ነው የሚያሳው፡፡
  • አንተም ቢሆን እኮ ለገንዘብ ምንም ደንታ የለህም፡፡
  • ስሚ የሙሰኞች ቀንደኛው መሆኔን ረሳሽው እንዴ?
  • እሱስ ልክ ነህ፡፡
  • ሌላው የሚገርምሽ ደግሞ ሠራተኛው ሁሉ ወዶታል፡፡
  • አንተንስ አባታችን ነው አይደል እንዴ የሚሉህ?
  • ሰው እኮ ወረተኛ ነው ስልሽ፡፡
  • እና በአንዴ ጠሉህ?
  • አንቅረው ነው የተፉኝ፡፡
  • የሰው ነገር እኮ ይገርማል፡፡
  • አሁን ምን እንደማደርግ ጨንቆኛል፡፡
  • ፖለቲካውን ጥርስህን የነቀልክበት አይደል እንዴ ምን አስጨነቀህ?
  • ሊተኩኝ ይችላሉ ስልሽ? ቀለል አድርገሽማ እንዳታይው?
  • ስማ በዚያ በሁለቱም በኩል በተሳለው ሰይፍ ቆራርጠህ ለምን አትጥለውም?
  • በምን በተሳለው?
  • በሐሜትና በአሉባልታ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ባቀረቡት ሪፖርት እየተገመገሙ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ያቀረቡት ሪፖርት በጣም ደካማ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • አሁን ካለው ለውጥ ጋር ሊቀጥሉ ይችላሉ ብዬ አላምንም፡፡
  • ምን እያላችሁ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር አስፈጽማለሁ ካሏቸው ሥራዎች ውስጥ አሥር በመቶውን እንኳን ማስፈጸም አልቻሉም እኮ?
  • እንደምታውቁት የሠራተኞቹ አቅም በጣም አነስተኛ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኛ ባደረግነው ማጣራት እርስዎ ራስዎ በቀን ውስጥ ከሁለት ሰዓት በላይ ሥራ ላይ አይገኙም፡፡
  • ያው ለተለያዩ ስብሰባዎች ስለምወጣ እኮ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ስብሰባ እኮ ከሥራ ሰዓት ውጪ ቅዳሜና እሑድ ይደረግ ተብሏል፡፡
  • ወሬ ሌላ ተግባር ሌላ አሉ፡፡
  • ምን እያሉ ነው?
  • እናንተስ አወራችሁ እንጂ መቼ ተገበራችሁት?
  • ክቡር ሚኒስትር የታቀዱ ፕሮጀክቶች እኮ በጊዜያቸው እየተተገበሩ አይደለም፡፡
  • ታዲያ እኔ ምን ላድርግ?
  • ክቡር ሚኒስትር የሁሉ ነገር ችግር እኮ ወደ እርስዎ ነው የሚያመራው፡፡
  • አልገባኝም?
  • መሥሪያ ቤቱን በአግባቡ መምራት ስላልቻሉ ነዋ ፕሮጀክቶቹ እየተጓተቱ ያሉት?
  • በእኔ ምክንያት አይደለም እኮ ፕሮጀክቶቹ የተጓተቱት?
  • ክቡር ሚኒስትር በእርስዎ ስንፍና ነው ፕሮጀክቶቹ የተጓተቱት፡፡
  • ሰነፍ ነህ እያላችሁን ነው?
  • በሚገባ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ ግን ይኼን አልቀበልም፡፡
  • ለምን?
  • ሠራተኞቹ እኮ ናቸው ሰነፎቹ፡፡
  • ሠራተኞቹ ሰነፍ የሆኑት ሲቀጠሩ በችሎታ ሳይሆን በወንዝና በጅረት መሥፈርት ስለተቀጠሩ ነዋ፡፡
  • ታዲያ ሠራተኞቹ ሲቀጠሩ እኔ አልቀጥር፣ ራሱን የቻለ ቅጥር ኮሚቴ አለ አይደል እንዴ?
  • ቢሆንም ሥራውን ስለማይቆጣጠሩት መሥሪያ ቤቱ እርስዎን ነው የሚመስለው፡፡
  • አሁን ይኼን ሁሉ ውርጅብኝ የምታወርዱብኝ ለምንድነው?
  • እርስዎ በቅርቡ መነሳትዎ አይቀርም፡፡
  • እ . . .
  • ያው እርስዎን የሚተካ ሰው እስክናገኝ ድረስ ለጊዜው ይቀጥላሉ፡፡
  • እና አንስታችሁ አውላላ ሜዳ ላይ ልትጥሉኝ?
  • ለእርስዎ ምቹ ቦታ ይዘጋጅልዎታል፡፡
  • ምን ልታደርጉኝ?
  • አምባሳደር!

[ክቡር ሚኒስትር ከአማካሪያቸው ጋር ሆነው ዓመታዊ የሠራተኞች በዓል ላይ ስለሚጠሩ ሰዎች እያወሩ ነው]

  • አንተ ባለፈው የተነጋገርነው ነገር ረስተኸዋል መሰለኝ?
  • የትኛውን ነገር ክቡር ሚኒስትር?
  • በአገራችን ላይ የመጣውን ለውጥ በማስመልከት የሠራተኞችን ሞራል ለማነሳሳት ዓመታዊ የሠራተኞች ቀን በዓል ይኑረን አላልኩህም እንዴ?
  • እሱማ ብለውኛል፡፡
  • ታዲያ በበዓሉ ላይ የምንጠራው የእንግዶች ስም ዝርዝር የታለ?
  • የራሳችንን ሠራተኞች አይደል እንዴ የምንጠራው?
  • እኔ የምልህ የቪአይፒ ሊስቱን ነው፡፡
  • እሱንማ ይኼው እንኩ፡፡
  • እነማን ናቸው እነዚህ ሰዎች?
  • አያውቋቸውም ክቡር ሚኒስትር?
  • ለመሆኑ የመጀመርያው ማን ነው?
  • እኚህማ ኢትዮጵያዊ ውስጥ አሉ የተባሉ ሳይንቲስት ናቸው፡፡
  • የምን ሳይንቲስት?
  • በዕፀዋት ምርምር የታወቁ ሳይንቲስት ናቸው፡፡
  • ከእሱ ቀጥሎ ያለውስ ሰውዬ?
  • እሱ ደግሞ የታወቀ የሕክምና ባለሙያ ነው፡፡
  • በዓሉ እኮ የሠራተኞች የደም ልገሳ ቀን አይደለም፡፡
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • ይኼኛውስ ማን ነው?
  • እሱ ደግሞ ታዋቂ የባንክ ባለሙያ ነው፡፡
  • ስማ የሠራተኞች ብድርና ቁጠባ ተቋም ለማቋቋም አስበን አይደለም እኮ በዓሉን ያዘጋጀነው?
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ለመሆኑ ይኼኛውስ ማን ነው?
  • በአገራችን አሉ የተባሉ አርክቴክት ናቸው፡፡
  • ሰውዬ ሕንፃችንን እናድስ ብዬሃለሁ እንዴ?
  • አሁን ግን ግራ አጋቡኝ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ እኮ ጥራልኝ ያልኩህ ቪአይፒ ሰዎችን ነው?
  • ከዚህ የበለጠ ቪአይፒ ከየት ይምጣ ታዲያ?
  • የቪአይፒ ትርጉሙን አታውቅም እንዴ?
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አገሪቷ ውስጥ ያሉት የቪአይፒ ሰዎች ማን እንደሆኑ ታውቃለህ?
  • እነማን ናቸው?
  • ሙዚቀኞች፣ የድራማና የፊልም ተዋናዮች፣ ተወዛዋዦችና ተመሳሳይ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ናቸው፡፡
  • እ . . .
  • እነዚህን ሰዎች እኮ ሕዝቡ በሙሉ ያውቃቸዋል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ የጥበብ ሰዎች ቪአይፒ አይደሉም እያልኩ ሳይሆን፣ እነሱ ብቻ ግን ቪአይፒዎች ሊሆኑ አይችሉም፡፡
  • ስማ የመንግሥት ትልልቅ ፕሮግራሞች ላይ እኮ ቪአይፒ ተብለው የሚጠሩት እነሱ ብቻ ናቸው፡፡
  • እርስዎ የሚፈልጉት ቪአይፒ ገብቶኛል ግን የቪአይፒ ትርጉሙ ይለወጣል፡፡
  • ትርጉሙ ምን ሊሆን?
  • Very Incompetent Person!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ኢንቨስተሮች አደጋ ሲገጥማቸው ድጋፍ ማድረግ የሚያስችለው መመርያ ተሻረ

በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ አደጋዎች በኢንቨስተሮች ንብረት ላይ አደጋ ቢከሰት፣...

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሥጋቶች

ዘ ኮንቨርሴሽን ላይ ‹‹What Next for Ethiopia and its...

ለውጭ ገበያ ሳይላክ ለቀረ ቡና ላኪዎች ታክስ እስከ ወለዱ እንዲከፍሉ ተወሰነ

ገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ቡና ላኪዎች የሚያቀርቧቸውን ሰነዶች መርምረው ወደ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...