በአማራ ክልል በወልዲያና በፍኖተ ሰላም ማረሚያ ቤቶች በተነሳ ‹‹ግርግር›› ማረሚያ ቤቶቹ መቃጠላቸውንና ሌሎች ጉዳቶችም መድረሳቸውን፣ የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ አስታወቁ፡፡
በማረሚያ ቤቶቹ ለተነሳው ግርግር ምክንያቱ በቅርቡ በፓርላማ የፀደቀው የምሕረት አዋጅ፣ እኛን ተጠቃሚ አያደርገንም በማለት የተቃወሙ እስረኞች ያስነሱት እንደሆነ አቶ ንጉሡ ገልጸዋል፡፡