የዳሸን ቢራ አክሲዮን ማኅበር በቦርድ አባልነት ሲያገለግሉ የቆዩትን አቶ በረከት ስምኦን፣ የጥረት ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ ታደሰ ካሳና አቶ ወንድወሰን ከበደን በአዳዲስ የቦርድ አባላት መተካቱን አስታወቀ፡፡
ሦስቱን ተነሺ የቦርድ አባላት የተኩት አዳዲሶቹ አባላት የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተርና የቀድሞ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ አህመድ አብተው፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥና ቀድሞ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ይናገር ደሴ (ዶ/ር) እና የጥረት ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስገፈጻሚና የቀድሞ የአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አምሳሉ አስረስ (ዶ/ር) ናቸው፡፡