Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርት45ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል

45ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል

ቀን:

ዘንድሮ ለ45ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚካሄደው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ይከናወናል፡፡ በሻምፒዮናው ከሰባት ክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ 551 ሴቶችና 756 ወንዶች የሜዳ ተግባራትን ጨምሮ ይፎካከሩበታል ተብሏል፡፡

ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ሚያዝያ 10 ቀን 2008 ዓ.ም. በብሔራዊ ሆቴል በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ በቅርቡ በአገር አቀፍ ደረጃ የተቋቋመው የፀረ አበረታች ንጥረ ነገር ተቋም (ብሔራዊ አንቲ ዶፒንግ ኦርጋኔዜሽን) ቁጥራቸው እስከ 50 ለሚደርሱ አሸናፊ አትሌቶችና ከሌሎችም እንዳስፈላጊነቱ በሚመርጡ አትሌቶች ላይ የአበረታች ንጥረ ነገር ምርመራ ይደረጋል፡፡ ለዚህ የሚያስፈልጉ የሕክምናና ለምርመራው የሚያግዙ ቁሳቁሶች በመንግሥት ልዩ ትዕዛዝ ተሟልተው እንዲቀርቡ የሚያደርግ አሠራር መፈጠሩም ተነግሯል፡፡ አትሌቶችና የአትሌት ተወካዮች ለምርመራው ሒደት ተባባሪ ሊሆኑ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

በሻምፒዮናው የታዋቂ አትሌቶችን ተሳትፎ በሚመለከትም ክልሎችና ክለቦች ባስመዘገቡት ዝርዝር መሠረት ተፈጻሚ እንደሚሆን ነው የተገለጸው፡፡ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች በስተቀር የተቀሩት ክልሎችና ክለቦች ተሳታፊ የሚሆኑበት የዘንድሮው ሻምፒዮና መክፈቻና መዝጊያው በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ቀጥታ ሥርጭት እንደሚኖረውም ተገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...