- Advertisement -

የአዲስ አበባ ከተማ ቁልፍ ቦታዎችን ይዘው የቆዩ ሁለት ባለሥልጣናት ተነሱ

ለአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት አዲስ ኃላፊ ተሾመ

ላለፉት አሥር ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቁልፍ ቦታዎችን ይዘው ሲመሩ የቆዩት አቶ ተወልደ ገብረ ፃድቃንና አቶ ኃይሌ ፍሰሐ ከሥልጣናቸው ተነሱ፡፡

አቶ ተወልደ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ዋና አማካሪ፣ እንዲሁም በከተማው ሙሉ ሥልጣን ያለው የአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ሲሠሩ ቆይተዋል፡፡

አቶ ኃይሌ ፍሰሐ ደግሞ አቶ መኩሪያ ኃይሌ ወደ ፌዴራል መንግሥት የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ ጊዜ ጀምሮ፣ የከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሠርተዋል፡፡

አቶ ኃይሌ እስካሁን የከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሲሠሩ የቆዩ ቢሆንም፣ በአዲሱ የአቶ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ካቢኔ ውስጥ ሳይካተቱ ቀርተዋል፡፡

አቶ ታከለ በሁለቱ ቁልፍ ቦታዎች ላይ አዲስ ሹመት ሰጥተዋል፡፡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ዋና አማካሪ ሆነው ከደቡብ ክልል ወደ አዲስ አበባ የመጡት አቶ ተስፋዬ ቤልጂጌ ናቸው የተሾሙት፡፡

- Advertisement -

አቶ ተስፋዬ የደኢሕዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩ ሲሆን፣ አሁን በአስተዳደሩ መዋቅር የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ ሆነው፣ በድርጅት መዋቅር ደግሞ የአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾመዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አወቀ ኃይለማርያም (ኢንጂነር) አቶ ኃይሌን በመተካት የአዲስ አበበ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል፡፡ አቶ አወቀ ወደ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሠርተዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ምክትል ከንቲባ ታከለ ሁለት ተጨማሪ ሹመቶች ሰጥተዋል፡፡ አንደኛው የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ዘሪሁን አባተ፣ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣንን በዋና ሥራ አስኪያጅነት እንዲመሩ ደግሞ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓት ኢንስቲትዩት ኤክስፐርት የሆኑት ወ/ሮ ዓለም አሰፋ ተሹመዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

አይኤምኤፍ ብሔራዊ ባንክ ገለልተኛ ሆኖ እንዲሠራ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አደረገ

‹‹ማዕከላዊ ባንክ ውሳኔዎቹን በመረጃ ላይ ብቻ ተመሥርቶ ካላሳለፈ አገሪቱንም ሆነ ኢኮኖሚውን አይጠቅምም›› ክርስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የአይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ ሰላም ማስከበር እንዲሳተፍ ምክክሩ መቀጠሉ ተገለጸ

የ38ኛው አፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ከ35 በላይ መሪዎች ይታደማሉ ተብሏል የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ ምክክሩ መቀጠሉን፣ ሒደቱ በመልካም ውጤት እንደሚቋጭ...

ገንዘብ ሚኒስቴር መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያለውን የዕዳ ሽግሽግ ድርድር አይኤምኤፍ አረጋገጠ

አበዳሪዎች የክፍያ ጊዜ ለማራዘም የአገሮች ፋይናንስ አቋምን ጨምሮ የሰላም ሁኔታ እንደሚጠና ተገልጿል የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ከቡድን ሀያ አባል አገሮች የጋራ ማዕቀፍ ሥር ከተካተቱ አገሮች...

ኢሕአፓ በኮሪደር ልማት ምክንያት ሜዳ ላይ ተጣሉ ላላቸው 455 አባወራዎች መንግሥት መልስ እንዲሰጥ ጠየቀ

ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ሊወስደው እንደሚችል ገልጿል ‹‹ሕጋዊ ከሆኑ አንድም ሰው እንዲጎዳ ስለማንፈልግ እናስተናግዳቸዋለን›› የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያከናወነ ባለው የኮሪደር ፕሮጀክት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የካቢኔ አባል የሆነ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ ስልክ ደውሎላቸው ሰሞኑን በተካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ ዙሪያ እያወሩ ነው]

ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡ ሰላም ሰላም፣ እንዴት ነህ? ቢዘገይም እንኳን አደረስዎት ክቡር ሚኒስትር። ለምኑ? ለፓርቲዎ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እንኳን አደረስዎት ማለቴ ነው። ቆየ እኮ ከተጠናቀቀ? አስቀድሜ ቢዘገይም ያልኩት እኮ ለዚያ ነው...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በውክልና ለግሉ ዘርፍ ለማስተላለፍ ያቀዳቸው አገልግሎቶች

የከተማው አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን ባሳለፈው ውሳኔ የተመረጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በሦስተኛ ወገን ለማሠራት የሚያስችለውን ደንብ በማፅደቅ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ታውቋል፡፡  አስተዳደሩ ደንቡን ከማጽደቁ አስቀድሞ በሦስተኛ ወገን...

የተገራ ስሜት!

እነሆ መንገድ ከስታዲዮም ወደ ጦር ኃይሎች። በጥበቃ የተገኘ ለበርካታ ዓመታት ያገለገለ ሚኒ ባስ ታክሲ ውስጥ ተሳፍረናል፡፡ ምሁር መሳይ ተሳፋሪ አጠገቡ ለተቀመጠ የዕድሜ እኩያው ማብራሪያ...

የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ አውጪዎች ችግር የት ጋ ነው ያለው?

በጌታነህ አማረ የአንድን አገር ኢኮኖሚ ችግር ለመፍታት መጀመሪያ ቁልፍ የሆነውን ነገር መረዳት በጣም ጠቃሚ  ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ቁልፍ ነገር ተብሎ የሚጠራው ‹‹ተርኒንግ ፖይንት›› ነው፡፡...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን