Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከጂቡቲ ለተመለሱ ዜጎች ሕክምና የሚሰጡ አራት የሕክምና ጣቢያዎች ተቋቋሙ

ከጂቡቲ ለተመለሱ ዜጎች ሕክምና የሚሰጡ አራት የሕክምና ጣቢያዎች ተቋቋሙ

ቀን:

ከጂቡቲ በመመለስ ላይ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሕክምና የሚሰጡ አራት የድንገተኛ ሕክምና ጣቢያዎች በድሬዳዋና አካባቢው መቋቋማቸውን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ እንዳስታወቁት፣ ከተመላሽ ኢትዮጵያዊያን መካከልም 74 የድንገተኛሙማን ታክመው 24ቱ ሲያገግሙ፣ የተቀሩት ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡

በምሥራቅረርጌ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት የተጎዱ ወገኖች የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ በሦስት ሆስፒታሎች አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ሲሆን፣ የፌዴራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርም ተጨማሪገዛና ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል::

በተመሳሳይ ባለፈው ሳምንት በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የተጎዱ ወገኖችን ለመርዳት ወደ ጅግጅጋ የተሰማራው የባለሙያዎች ቡድን ጉዳት ለደረሰባቸው 128 ሰዎች የሕክምና አገልግሎት መስጠት ችሏል፡፡

ከተጎጅዎቹ መካከልም ግማሽ ያህሎቹ የጭንቅላት፣ የደረት፣ የሆድና የደረት ቀዶ ጥገናክምና የተደረገላቸው መሆናኑን የሕክምና ቡድኑ መሪ / ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል፡፡ የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጂጋ ከማቅናቱ በፊትም በድሬዳዋ ከተማ በተፈጠረው ግርግር ጉዳት ለደረሰባቸው ተጎጅዎችም የሕክምና ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡

እንደ / ብርሃኑ ገለጻ፣ የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ ማቅናቱ ለተጎጅዎች የሕክምና ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር በማኅበረሰቡ ዘንድ መረጋጋት እንዲፈጠርና የአካባቢው ጤና ባለሙያዎችም ወደ መደበኛራቸው ተመልሰው የሕክምና አገልግሎታቸውን በተቀላጠፈ መልኩ እንዲሰጡድል እንዲፈጠር አድርጓልም ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በተፈጠረው ችግር ምክንያት መድኃኒታቸውን ያቋረጡሙማን ወደ ቀድሞ ክትትላቸው እንዲገቡም ተደርጓል፡፡

አሥር የቀዶ ጥገናኪሞች፣ ሦስት አንስቴዮሎጂስቶች፣ ስድስት አንስቴቲስቶችና አራት የኦፕሬሽን ክፍል ነርሶች፣ በአጠቃላይ 23 የጤና ባለሙያዎች በሕክምና ድጋፉ ተሳትፈዋል፡፡ ቡድኑ ከጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከየካቲት 12 እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የተወጣጡ 24 የጤና ባለሙያዎችን ያካተተ ነው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...