- Advertisement -

ለሚቀጥለው ዓመት ለ40/60 ቤቶች ፕሮግራም 11 ቢሊዮን ብር ተጠየቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ፣ በሚቀጥለው በ2011 ዓ.ም. ለሚያካሂዳቸው 40/60 ቤቶች ግንባታ 11 ቢሊዮን ብር በጀት ጠየቀ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይህንን ገንዘብ ያቀርባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣  የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ለቤቶች ግንባታ የሚሆን 38 ሔክታር መሬት ማስረከቡም ታውቋል፡፡

ግንባታዎቹ የሚካሄዱት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ቦሌ አራብሳ አካባቢ እንደሆነ፣  ኢንተርፕራይዙ ከሚመለከታቸው የአስተዳደሩ መዋቅሮች ጋር በመሆን የወሰን ማስከበር ሥራ እያከናወነ መሆኑ ታውቋል፡፡

በ2011 ዓ.ም. በ38 ሔክታር መሬት ላይ ግንባታቸው የሚከናወነው 8‚428 ቤቶች ሲሆኑ፣ በብሎክ ደረጃ ደግሞ 54 ሕንፃዎች ናቸው ተብሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት በ40/60 ፕሮግራም የ38‚200 ቤቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 17‚700 ቤቶች የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑባቸው መሆኑን ከኢንተርፕራይዙ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፈቀዳል ተብሎ የሚጠበቀው 11 ቢሊዮን ብር፣ የተጀመሩትን ሥራዎች ለማጠናቀቅና አዲስ የሚካሄዱትን 40/60 ቤቶች ግንባታ ለማስጀመር ነው ተብሏል፡፡

- Advertisement -

አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) በቀጥታ ሊከታተሏቸው ካቀዷቸው ፕሮጀክቶች መካከል መሬትና መሬት ነክ ሥራዎች፣ የቤቶች ግንባታና የውኃ ፕሮጀክቶች ግንባር ቀደሞቹ ናቸው፡፡

በመሬት ዘርፍ ለውጥ የሚያመጡ ሥራዎችን ለማካሄድ በቅድሚያ ሪፎርም ለማካሄድ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን፣ የሪፎርሙ አባል የሆነ የመሬት ኦዲትም በቅርቡ እንደሚጀምር መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በውኃ ዘርፍም የአሠራር ለውጦች እየተደረጉ ሲሆን፣ በቤቶች ግንባታ ዘርፍም በርካታ ለውጦች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተለይ በ20/80 እና በ40/60 ቤቶች ፕሮግራም በርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ተመዝግበው እየተጠባበቁ ቢሆንም፣ ግንባታው በዕቅዱ መሠረት መሄድ ባለመቻሉ ቅሬታዎች በብዛት እየቀረቡ ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት ኢንተርፕራይዙ ግዙፍ ግንባታዎችን ለማካሄድ በሚያስችል ደረጃ ራሱን እያደራጀና የሰው ኃይሉንም እያሟላ መሆኑን ይናገራል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

በተያዘው ወር መጨረሻ  አዲስ ፖስፖርትና ቪዛ  ይፋ ይደረጋል ተባለ

በውጭ አገር የሚታተመውን ፓስፖርትና አገሪቱ ለውጭ ዜጎች የምትሰጠውን ቪዛ በአዲስ ይዘትና ኅትመት በአገር ውስጥ ታትሞ በተያዘው ወር የካቲት 2017 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽንና ዜግነት...

በውጭ አገር ለሚሰጥ ሕክምና የአገር ውስጥ ተወካይ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚያስገድድ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

የጤና ሚኒስቴርን ፈቃድ አግኝተው በውጭ አገሮች የሕክምና አገልግሎት ተቋማት የሚታከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የሕክምና አገልግሎት ጥራት ደረጃ ጉድለት፣ የሕክምና ስህተት ወይም የሙያ ግድፈት ቢፈጸምባቸው፣ የውጭ ሕክምና...

በአማራ ክልል የአሽከርካሪዎች ዕገታን መደበኛ የሥራ ቦታ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው መበራከቱ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የአሽከርካሪዎች ዕገታ በአሁኑ ወቅት ክፍት የሥራ ቦታ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ፡፡ አሽከርካሪዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና ሲያዙም በአግባቡ በሕግ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ከተወዳዳሪው ኩባንያ ቅሬታ እየቀረበበት መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያ ቴሌኮም ጉልህ የገበያ ድርሻ እያለው አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ለተወዳዳሪው ኩባንያው ውድድሩን አስቸጋሪ ስላደረገበት፣ ‹‹መንግሥታዊ ኩባንያው ዋጋ እንዲጨምር መገደድ አለበት የሚል የቅሬታ ጥያቁ...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን