Saturday, December 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ይድረስ ለሪፖርተርሰዎች ለምን ለውጥን ይሸሻሉ?

ሰዎች ለምን ለውጥን ይሸሻሉ?

ቀን:

ለውጥ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ ፍራ አለው። የዛሬይቱ ለም ማበራዊ፣ ባህላዊ፣ ይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ፣ መልክዐ ምድራዊ ወዘተ ሁናቴ መነሻ ሲኖረው፣ በጊዜ ሒደት ውስጥ ታሽቶ ዛሬነቱን ሊያገኝ የቻለው በለውጥ ጉልበት ነው።ለውጥ በፈጣሪ የተዋቀረ ት እንጂ ከፈጣሪ ጋር በተቃርኖ የቆመ ት አይደለም። የለውጥ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ጉልበቱ ደግሞ ጊዜ ነው።ለምና ቷ ከተቆረቆሩ ጊዜ ጀምሮ ለውጥና የለውጥ እንቅስቃሴና እሳቤ አብሮዋት የዘመኑ ዕድሜ ጠገብ ክንውን እንጂ ለውጥ ጊዜ አመጣሽ ሳቤ አይደለም፡፡ በመሆኑም ለውጥና መለወጥ የለም ወግ ነው። አንዳንዱ የለም ለውጥ አዝጋሚ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፈጣን ነው። ሁላችን እንደምንታዘበው ነገ የሚባለውን ማንነትና ምንነት ለመፈጠር ለምና ሞላዋ በጊዜ ውደት ውስጥ መናጧን ዛሬም ቀጥላለች ነገም  ትቀጥልበታለች። ነገን ማየት የሚወድ፣ በነገው ለም ላይ የተሻለ ሆኖ መገኘትን የሚመኝ ሁሉ ዛሬውን በጊዜ ውስጥ አኑሮ፣ ዛሬን  ስለነገ ዋጋ ከፍሎ ሊኖር ይገደዳል።

አንዳንዱ የለም ክውኖች በጎ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ በጎ ያልሆ ክስተቶችዓለም አስተናግዳለች፣ እያንዳንዱ ክንውን ጊዜ በሚባለው አዙሪት ር የተቃኘ በመሆኑ፣ ፍጥረት ሁሉ የለውጥ ተጠቂ ሆኖ የዕድሜውን ዙረቱ ይኖረዋል። ፍጥረት ሁሉ ጊዜው የሚያደገውን ይሆን ዘንድ ግድ ሆኖበት ዘመኑን አንድ ብሎ መቁጠር ይጀምራል፡፡ ተወለድ ብለን ለመቁጠር ጀምረን ሳንጨርስ ከጥቂት መታት በኋላ ሞተን በማጠቃለያ ዜናነት እንሆናት ዘንድ እንገደዳለን። ሰው ከፍጠረታቱ ሁሉ ልዮ የሚያደረገው ጊዜ የሚያመጣውን ለውጥ ለመቀልበስ ከፍተኛ ግብ ግብ ውስጥ መግባቱ ነው። በእርግጥም ሰው ጊዜና ዘመን የሚያመጡትን ለውጦች ለማስቆም ባይችልም በተወሰኑ ሁናቴ ለመዘግየት መቻሉ ግን ትልቅ ቁምነገር ነው። ሕይወት የሚጀምርበትና የሚቆምበትን ጊዜ መለ የሚካሄደው ሙከራ እጅግ አድካሚ ነው፡፡ ሰው ግን ይህንን ይለውጠው ዘንድ ከሙከራ ጥበብ ውስጥ ገቶ ዘወትር ይታገላል። ይህ ግብ ግብ ጊዜን በመቆጣጠር ረገድ ምን ያህል ከፍታ ላይ ይደርስ ይሆንን?  የትግሉን ውጤት ጊዜው ራሱ ይነግረናል። ለእኔ ጊዜ በለማችን የለውጥ ሒደት ውስጥ እምብርት እንደሆነ ይሰማኛል።

ይህ የለውጥ እውነታ እንዳለ ሁላችን ብናምንም ለውጥን ግን አናምናት። ከዚህ የተነሳ ለውጥን በብዙ መንገድ ስንሞግታት፣ አንዴ ሽቅብ አንዴ ቁልቁል ስንገፋት እንስተዋላለን፡፡  ለውጥ ግን ታላቅ ይል ናትና ብርታቱዋን በጊዜ ውስጥ ትገለጣለች። ለውጥን ማዘግየት ይቻል ይሆናል፣ የለውጥን ፍላጎት አቅጣጫ ወደ አልተፈገ መስመር መቀልበስም ይቻል ይሆናል ነገር ግን ለጡን ማስቀረት ከቶውኑ የሚሆን ጉዳይ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የመደብ ትግል፣ የነነት ጥያቄ፣ ብት ክፍፍልና ፍትዊነትና ሌሎች የተለያ ጥያቄዎችን ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ በማበረሰቡ ልብ ውስጥ ሲንከባለል  የኖረ ጥያቄ ነው። ማበረሰብ ጥያቄን አዝሎ በዝምታ ሲጓዝ ከርሞ ጊዜ የወለዳቸው ግለሰቦችና ቡድኖች በማበረሰቡ ውስጥ ያለውን ጥያቄ ጉዳያቸው አድርገው ድምቸውን ከፍ አድርገው ሲያሰሙና ማበረሰቡም በውስጡ ላለ ብሶት ምላሹን ሲቸር ለውጡ በድንገት ብርቱና ጉልበታም መሆን ይጀመራል። ለውጡን ሊመሩ ድምቸውን ከፍ አድርገው ያሰሙ ሰዎች ግን ከማበረሰቡ ድጋፍ ብቻ እንደሚያገኙ ብቻ አስበው የጀመሩ እንደሆነ ግን እሳቤቸው ልክ አለመሆኑን የሚረዱት አፍታም ሳይቆ ነው። ለውጥን የጀመሩ አካላት ድጋፍም፣ ተቃውሞም ከማበረሰቡ ሊገጥማቸው እንዲችል ከወዲሁ መገንዘባቸው መልካም ነው። ከቀደም  “ወርቅ ቢያነጥፉለት. . .”  እንዳለው “ቆራጡ” መሪ ማበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ ካልደገፈን ብሎ ከሙግት ውስጥ ራስን መዶል ለወድቀት መጀመሪያ ይሆናል። ማበረሰብ የገዛ ራሱ ምርጫ ፍላጎት አለው፡፡ አንዱ ሲወድ ሌላውን ሊጠላም መብት አለው፡፡ አንዱ የማኅበረሰብ ክፍል የሚያድቀውን ሌላኛው ሊያረክሰውም ይችላል

መሪነት እነዚህን የተለያዩ የማይገናኙ የሚመስሉ ጽንፎች ባሉበት ለውጥን መጫር ነው፡፡ መሪነት ስለለውጥ ነው። መሪ ግልጽ የሆነ ተቃውሞ ከብዙኑ ቢገጥመው ምን ሊያርግ ይገባል? ተቃውሞ በብዙ መልክ ሊገለጽ ይችላል። በእኛ አገር ተቃውሞ ቤት በመቀመጥ፣ ባልስማማበትም “ንብረት በማውደም”፣ ላማዊ ልፍ ላይ በመሳተፍ፣ የተቃውሞ ጽሑፎችን በማሰናዳት፣ በሕቡ በመደራጀት ጥቃት በመፈጸም፣ ምርታማነትን ሆን ብሎ በመቀነስ፣ የው ምንዛሪ እጥረት አገሪቷን እንዲያዳክማት ማድረግ፣ ከገዢው መንግት ጋር ወገንተኛነት ያላቸውን ሰዎች በማበራዊ ተሳትቸው ሆ ብሎ በማግለል፣ ለም አቀፋዊ ተቀባነትን በማሳጣት፣ በአገር ውስጥ ማበረሰቡ መረጋጋት እንዲያቅተው በማስቻል፣ ማበረሰቡ ቁጣውን በገዥው ላይ እንዲያሳይ በማነሳሳት፣ የገዥውን አመራሮች ግለስባዊ ቅቡልነት በማጎደፍ ተቀባይነት በማሳጣት፣ መሪዎች እርስ በራስ እንዳይተማመኑ መረጃዎች ከመካከላቸው አፈትልከው የሚወጡበትን መስመሮች በመገንባትና በሌሎች በርካታ መንገዶች ተቃውሞን ማበረሰቡም በጋራም ሆነ በተናጠል ያካሄዳል፡፡ ወደፊትም ያካዳል። ይህንን ተቃውሞ የሚቋቋም አመራርና ሥርዓት መገንባት የመሪ ትልቁ ድርሻ ነው። አመራርና ሥርዓት ደግሞ የሚገነባው ችሎታንና ታማኝነትን ባማከለ አካድ እንጂ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ስለትምህርት እንዳሉት ከችሎታ ይልቅ ታማኝነትን በማስቀደም መሆን ያለበት አይመስለኝም። ችሎታ የሌለው ታማኝ ራ መራት አይቻለውም። በመሆኑም ራቸው ሒደት ለሚገጥማቸው ችግሮች ሁሉ መፍትሔ ለመስጠት የማይችሉ ታማኞች ይሆናሉ። ብልህ መሪዎች ለሚፈለጉት ና ውጤት የሚመጥን ችሎታ፣ ጥበብ፣ ተነሳሺነት ያላቸውን ግለሰብና ቡድኖች ከዙሪያቸው ያኖራሉ፡፡ እነዚህ ቡድኖችና ግለሰቦች የሚሠሩበትን ሕጋዊ፣ ፍትሐዊ፣ ግልጽ፣ አሳታፊ፣ ከአድሎ የፀዳ ሥርዓትን ደግሞ ይገነባሉ።

ታዲያ ሰዎች ለውጥን ስለምን ይፈሩዋታል?

 ለውጥ ሲመጣ ከዚህ ቀደም በልጣን ላይ ያሉትን አካላት የውሳኔ አቅምና ጉልበት ከንቱ ስለሚያደርግልጣን ኮርቻ ላይ ያሉ ሰዎች ለውጥንና የለውጥን እንቅስቃሴ አጥብቀው ይፈራሉ። ይህ ፍርኃት በፖለቲካው ት ላይ ስላላቸው አቅምና ተሰሚነት ብቻ ሳይሆን በገዛ ሕይወታቸውና ኑሮዋቸው ላይ የሚኖራቸውን ግላዊ ውሳኔን ጭምር እንደሚቀይረውም ጭምር ከሕይወት ተሞኩሯቸው ስለታዘቡ በእጅጉ ይጋሉ። ከዚህም የተነሳ ለለውጥ መነሻ ሊሆኑ ይችላሉ ያሏቸን ግለሰቦችና ቡድኖችን በማጥፋት ራ ላይ ዘወትር ይጠመዳሉ። ቋኞችና ገዢዎች ሁሉ ሊገነዘቡት ያልቻሉት ትልቅ ቁምነገር የሚያሳድዳቸው የገዛ ታቸው እንጂ የሚያሳድዳቸው ሌላ አካል የለም። ይህ እውነት ጨቋኞች ላልሆኑት ሁሉ የሚቅ ነው።

ብልህ መሪዎች በለውጡ ሳቢያ ሥልጣናቸውንና ምቾታቸን ጡ አካላት የገዛ ምርጫቸውን እንዲወስዱ ዕድል የሚሰጥ እንጂ ከዚህ ቀደም በገዛ ዘመናችን እንዲሁም በታሪካችን እንዳሰተዋልነው ከልጣን የወረዱ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ወደ ማጎሪያ ጣቢያ መውሰድ ወይንም የመኖር መብታቸውን ማሳጣት መፍትሔ አይደለም። የለውጥ አቀንቃኞች እንዲህ ያለውን ዕርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱት ከፍርኃት የተነሳ ነው። የመሪ ድርጊት መነሻው ፍርኃት ሳይሆን የለውጡን ሞተር ያንቀሳቀሰበት ዓላማው ነው። በመሆኑም ብዙኃኑን ሊጠቅም የሚችለውን ዓላማውን ለሰፊው ሕዝብ ማሳወቅና ደጋፊ ማበራከቱ መልካም ነው። ስለሆነም ሕዝብ ወደ ተሻለ የኑሮ ግንባታ እንዲገባ  ሁሉን አሳታፊ፣ ግልጽና የሚለካ ዕቅዶችን በማውጣት ሰፊው ሕዝብ የቅዱና የሒደቱ ባለቤት ማድረግ ያስፈልጋል።

የማይታውቀው ጉዞ  ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ በጎዳናዎ ላይ በተንቀሳቃሽ ነጋዴዎ ከሚሸጡ ዕቃዎ መካከል በአንዲት ዕል ላይ ይኔ አረፈ፡፡ ዕሉ ላይ አንዲት የምታምር ትንሽ ልጅ የእናትዋን ጫማ ተጫምታ መንገድ ጀመራ ይታያል፡፡  ከዕሉ አናት ላይ “ወደ የት እንደምድ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ጉዞ ጀምሬለሁኝ” ይላል። ዕሉ ከመልክቱ ጋር በመመሳሰሉና በመግጠሙ እየተገረምኩኝ እኔም ጉዞን ቀጠልኩኝ።  ሕዝብ የሚመራው ግልጽ በሆነ ራእንጂ በሚያማልሉ ብዙ ቃላት አይደለም። ራይ የሌለው መሪም ሆነ ሕዝብ ወሎ አድሮ መስመሩን መሳቱ አይቀሬ  ነው። ከዚህም በተጨማሪ የውጤታማ መሪነት መረቱ ባለራይ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለያዘው ራይ የሚመጥን ዕቅድ፣ ዝግጅት፣ ሥልት፣ አደረጃጀትን ቁርጠኝነትንና ሌሎችን ግብዓቶች ያለ ምንም ችግር ሲያሳጥ ነው። ራይ የሌለበት ቡድንተኝነት ሆነልጣን ዘመን ያለፍሬ መደምደሙ ሳያንስ አክሳሪም ጭምር ነው። ታሪካችን ይህንን ደጋግሞ ይዘክረዋልና ልብ ያለው ልብ ይበል።  

በአገራችን “ከማያውቁት መልክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል” ይባላል። ማበረሰቡ ከመልክ ይልቅ ሰይጣንን ወዶና አስበልጦ ሳይሆን ማበረሰቡ በአባባሉ እንዲተላለፍ የፈለገው የሚሻለውን መልክ እናውቀው ዘንድ እንደሚገባ ለማሳብ፣ እርሱን ባናውቀው ግን ቢያንስ ሰይጣኑን አውቀነዋልና ከሰይጣናዊ ተግባሩ ልንገታው ይቻለናል፣ ከሰይጣናዊ ተግባሩ ልንገታው ካልተቻለን ደግሞ ክፋቱንና ይጣናዊነቱ  እንዳይጎዳ እንጠነቀቀዋለን የሚል ይመስለኛል። ይህ ሁሉ ሐተታ አንድ ነገር ለማስቀመጥ ነው፡፡ ይኸውም መሪነት ያለ ራይ ከንቱ ድካም ነው። ይህ ራይ ደግሞ  ግልጽ የሚለካ፣ ሒደቱ ተጭባጭ፣ የማያሻማ፣ በጊዜ መርሃ ግብር የተዋቀረ መሆን ይኖርበታል። ብሩህ መሪዎች የሚከተላቸውን ብዙ መሪዎች ለማፍራት ከራዕያቸው ባሻገር ሒደቱን ግልጽና ሁሉም ሊገነዘበው እንዲ ያደጋሉ።

ጉዱ ካብ ዕዳዎች  ሕዝቦች ያልታሰበና ያልተጠበቀ ድንገታዊ ክስተትን ማስተናገድ ብዙ አቅም የላቸው። በአገራችን ለተከሰቱት ለውጦች ድንገታዊ ዱብ ዕዳ የሆብን ብዙ ታሪካዊ ክስተቶች አሉን። የአ ቴዎድሮስ፣ የግርማሜዎቹን እንቅስቃሴ እንደ አብነት ማንሳት ይቻላል።  ሁለቱ የግርማሜ ልጆች በወቅቱ ንጉን ለማውረድ የሚያስችል ማበረሰባዊ አደረጃጀት፣ እሳቤና እምነት ባልዳበረበት፣ በመሪው የሚምል ሰፊ ማበረሰባዊ ይል በተንሰራፋበት ሁናቴ ሳይደራጁና ነገሩን በጥልቀት ሳይመክሩ የተፈጸመ እንቅስቃሴ በመሆኑ ለተነሱለት ላማ ሕይወታቸውን ገብረው ዛሬ ድረስ ደማቅ ታሪክ ባለቤት ቢሆኑም፣ ሊሞቱለት የፈቀዱለት ለውጥ ግን መጎናጸፍ ሳይችሉ ጎድለዋል እነዚህ ብርቅ የግርማሜ ፈርጦች ከማበረሰቡ ቀድመው ነቅተው፣ ማበረሰቡን ሳያነቁና ሳያላምዱ ለውን ሊያበስሩ ከማደሪያቸው እንደወጡ ያስቀራቸው ለውጡን ሊደግፍ የሚችል የለውጡ ባለቤት የሆነው ማበረሰብ በሰፊው ስላልተሰናዳ ነው። መሪዎች ለውጥን በር ይዘው ከርመው በአንዲት ጀንበር ወደ በረሰቡ ሊያሰርፁት መሞከር የለባቸውም፡፡ ሩ የለውጡ አቀንቃኞቹ ማንነት እንጂ ለውጡ መሆን የለበትም። የንጉዊው ት ሲገረሰስ ለውጡን ሲያቀነቅኑ ያልነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ማግኘት አይቻልም። ለውጡ በገጠር፣ በከተማ በሁሉም ፍራ እንደ መት በል ድግስ በየቦታው ይሸት፣ ይናኝ እንደነበር በወቅቱ ባንወለድምሪክ ተረናል። ደርግ የዚህ ለውጥ አስጠባቂ መስሎ የለውጡን አቀንቃኞች የነበሩትን ወጣቶች በጠራራ ፀሐይ ፈጅቶ የለውጥ ቀማኛነቱን በታሪክ ድርሳን ላይ አስፍሮም አልፎዋል፡፡ መሪዎች ሊያመጡ የሚወዱትን ለውጥ ማኅበረሰቡ እንዲገነዘብ በተለያዩ መድረኮች መረጃዎቻቸውን በጥንቃቄ ያስተዋውቃሉ፡፡ ሒደቱም ወደማያስፈለግ አቅጣጫ እንዳይሄድባቸው ነቅተው ይከታተላሉ። 

በእንቁጣጣሽ ሁሉ ነገር ል ይመስላል፡፡  ለውጥ ማለት አንድን ነገር የተለየ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ምን ያህል ል ነው? አንድ መሪ የሚያመጣውን ለውጥ ሰዎችስ ምን ያህል ልነቱን ይረዱለት ዘንድ አድርጎዋል? ለተመዘገበው ለውጥስ ማኅበረሰቡ ምን ያክል ቀኝ እጃቸውን ይሰጣሉ? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት። ሰው በተፈሮው ለማዳ ፍጡር ነው፡፡ የለመደውን ቀ ጥሎ ወደማያውቀው ፍራ ሊነጉድ ሲነሳ መላ ነቱ በጭንቀት ይተራመሳል፡፡ውን ጥሎ ርቆ ተመችቶት እየኖረ እንኳን ያንን የጥንቱን ሕይወት እንደሚናፍቅ ሲያወራ ስተዋልም ድንገት ወደ ቀድሞ ቀው ተመለስ ባል አይ አሁን እዚሁ ተላምጄዋለሁኝና እንደገና ደግሞ ሀ ሁ ልል ነውን? ማለቱ አይቀርም። ሰው በብዙ መልኩ ለውጥ አይመቸውና የለውጥ አቀንቃች ለለውጥ ሲነሱ ለውጡ የማበረሰቡን መሠረታዊ መቀመጫ የማይንድ አለመሆኑን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን በተግባር ማሳየት ይኖርባቸዋል። የኢትዮጵያ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አመድ (ዶ/ር)ረቤታቸውን እማሆይ ቤት ማደስ ከአንድ ግለሰብ ባለፈ ለአዲስ አበባ ነዋሪ የሚያስተላልፈው መልክት ትልቅ ነው።  እኔ እንደምረዳው እየመጣ ያለው ለውጥ ከቀዬህ የሚያፈናቅልህ አይደለምና ከሥጋት ውስጥ አትግባ እንደማለትም ጭምር ነውእየመጣ ያለው ለውጥ ቤትን የሚያድስ፣ ተስፋን የሚያለመልም ነው የሚለውን መልክት በጉልህ ለሰፊው ብረተሰብ በቀላል ተግባር ማስተላለፍ ተችሏል። መሪዎች ሁሉን ነገር በእኔ የሥልጣን ዘመን ካልለወጥኩኝ ሙግት ውስጥ መግባት ታላቅ ኪሳራ መሆኑን የቋራው ቋጥኞችን ለዘላለሙ ከተንተራሰው ጀግና መማር ይቻላል። መሪዎች በገዛ ዘመናቸው ሊለውጡ በተነሱት ጉዳዮች ብቻ ላይ አትኩሮቶቻቸውን ሊያውሉ ያስፈጋል፣ ስለለውጥ ተሎ የሚደረግ ለውጥ ሁሉ ውጤት አያመጣምና ዋና ጉዳዮች ላይ አትኩሮት ቢሰጥ ለውጡን እውን ማድረግ ብቻ ሳይሆን ማስቀጠልም ያስችላል።

የጥንቱን ውብት መቼም ለውጥ ሲባል  ወደ አዕምሮዋችን የሚመጣው ከቀሞ የተለየ በመሆን የጥንቱን ጥሎስ፣ የትላንቱን ወደኋላ አሽቀንጥረን በመጣል ወደ ፊት ስለመገስገስ እንደሆነ የታሪክ መረጃችን ይነግረናል። ይህ ይነት ለውጥ ግን ለውጥ ብቻ ሳይሆን አፍራሽም ሊሆን እንደሚችል መገዘቡ መልካም ነው። ድሮ ድሮ ልጅ እያን ለበዓል አዲስ ልብስ ስንለብስ፣ አዲስ ጫማንም ስንጫማ ከዚህ ቀደም የለበስናቸውን፣ ለብሰንም ያጌጥንባቸውን ልብሶችና ጫማዎች ሁሉ ረስተን በአዲሶቹ ብቻ ተሽቀቅረን በጓደኞቻችን ፊት ደምቀን መታየቱን እንወዳለን፡፡ ይህ  ደስ የሚል ልጅነት ጊዜ ነው።  አገር እንዲህ ባለ የልጀነት ልቡና መመራት ከጀመረ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ቀስ በቀስ እያየለ እንደሚሄድ ከእኛ ከሐበሾች የተሻለ የሚረዳው ላይኖር ይችል ይሆናል፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ የአገራችን ታሪክ ይኼና ከዚህ የከፋ ሁናቴን የያዙ መስተጋብሮችን በውስጡ ይዘዋል። በአገራችን ውስጥ የተከሰቱት ለውጦች የትላንትናውን ሥርዓት የማይቀበል ብቻ ሳይሆን የትላንትናውን ሥርዓትን የመሩ ኃይሎችን በሕይወት እንዳይኖሩ ሕይወታቸውን የቀጠፈ፣ የመንቀሳቀስ መብታቸውን ያገደ የትላንቱን ቂም በቀል በመመለስ ለአዲስ ቂም እርሾ የተወ ነበር።  ብልህ መሪ ስለነገ ትላንቱን በአስተማሪነቱ የሰነቀ፣ የትላንቱን ከፍታ እንደ መነሻ የወሰድ፣ ጥፋቱን ላለመደገም የቆረጠ ካልሆነ በቀር እንደ ትላንቱ ከሾካማ ጭቃ ውስጥ ራሱን መዶሉ የግዱ ይሆንበታል።

የከረም ቁርሾና ቁጣ ዛሬ ላይ የታፈነ ቁርሾና መከፋት ተዳፍኖ ብናየውም አንድ ቀን አንዳች ፋስ ሲያገኘው ረመጥ ሆኖ ሊፋጅ እንዲችል መረዳት መልካም ነው።  ሁሉ ነገር ሲዳፈንና ሲሸፈን  የተረሳ፣ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ የሆነ፣ የልጣም እርካቡም  የተደላደ ይመስላል። ነገር ግን  አንድ ቀን ልከኛ ንፋስ የምትመስል ሽውታ አመዱን የገለጠችው እንደሆነ፣ ሰዎችን እንዲደራጁለውጥን እንዲሹ ያደረገች እንደሆነ  የከሰመውና የተዳፈነው እሳት ትልቁን ጫካ የሚበላ ታላቅ ነበባል ወደ መሆን ሊለወጥ እንዲችል መገነዘቡ መልካም ነው። ስለሆነም መሪዎች ነገን ለመገባት ከመነሳታቸው አስቀመው በሕዝቦች ዘንድ ያለን የትላንቱን ቁርሾ፣ ጥላቻ መፈወስ ይኖርባቸዋል። የከረመ ቁስል ሊከፈት ይችላል፡፡ የትላንትናው ታሪካዊ ስህተቶች በዛሬ ትውልድ እንደገና ሊታሰቡበት የሚቻላቸውን ሁናቴ ሊያገኙ ይችላል። ታዲያ መሪዎች ቆም ብለው የተዳፈነን ነገር ለመካድና እንዳልነበረ እንድንቆጥር ‹‹በቃ እርሳው›› አካሄድን ለማራመድ ቢወዱ ከትልቅ ኪሳራ ውስጥ ራሳቸውን ሊዶሉ ጀምረው እንደሆን እንጂ በመንገዳቸው ትርፋማ አይሆኑም።  ከዚህ ይልቅ የትላንቱን ስተት እንዳይደገም በብዙ ጥንቃቄ ሥት ዘርግተው፣ በሕግ አግባብና ማዕቀፍ ነገሩን አስከበረው ማበረሰባዊ ፈውስ ፈጥረው ወደፊት ጉዞዋቸውን ሊቀጥሉ ያስፈልጋቸዋል።

ለውጥ አደጋም አለው፡፡ ብዙ ሰው ለውጥን የሚሸሽበት ምክንያት ለውጥ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ጉዳትም ሊያስከትል የሚችል በመሆኑ ነው። አንዳች አዲስ ግኝት ሲፈጠር የቀድሞው ግኝት መንገዱንና ፍራውን ለአዲሱ መሰጠቱ ግልጽ ነው። በዚህም ዎች ራሳቸውን ከዘመኑ ግኝት ጋር ካላዘመኑ በቀር አዲሱ ግኝት ተግባራዊ ሲሆን ራቸውን ጥቅማቸውን ሊነጥቃቸው እንዲችል ስለሚረዱ ለውጥን በእጅጉ ይፈሩታል፡፡ ለውጥን መፍራት ብቻ ሳይሆን የለውጡ ጽኑ ባላንጣዎች ይሆናሉ።  ስለዚህ ለውጥን የሚያራመደው አካል ወይንም መሪ ለውጡን እውን ማድረግ በሚያደርግበት ጊዜ እያንዳንዱን የለውጥ ሒደት ግልጽ፣ ተአማኒነት ያለው፣ ፈጣንና ፍትዊ ሊያደገው ይገባል።

ለውጥ ሲመጣ በማኅበረሰቡ ዘንድ ያለው ስሜት የተተራመሰ ስሜት መፍጠሩ ነው፡፡ ማኅበረሰባዊ መረዳት በማሳደግ ለውጡን እንዲረዱና እንዲገነዘብ ካልተደረገ በቀር ማኅበረሰቡ ሕግ አልባ ወደመሆን በቀላሉ ሊሸጋገር ይችላል። ከዚህ ውጪ በለውጡ ምክንያት ተንሳፋፊ እሆን ይሆንን? የሚል ፍርኃት ያደረባቸው ግለሰቦችና ቡድኖችም በተናጠልና በቡድን የለውጡን ሒደት ለማደናቀፍ መሞከራቸው አይቀርም። የተጀመረው ለውጥ እነርሱን ከምቾቶቻቸው እንደሚያፈናቅላቸው፣ ጥቅማቸውን እንደሚነካባቸው ከመሰላቸው ለውጡ በማኅበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዳይኖረው ሰፊ የማጥላላት ዘመቻም ውስጥ ይገባሉ። ብልህ መሪዎች ይህንን ብዥታ ለማጥራት ብሎም የሰዎችን አቅም ለማደራጀት ሰፊና የተጠናከረ ሥልጠና፣ ለውጡን የማስተዋወቅ ተግባር ውስጥ ይገባል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስለሚያከናውኗቸው ዕቅዶችና ዓላማዎች ከባላንጣዎቻቸው ይልቅ ሥፍር ቁጥር መረጃዎችን ያሰራጫሉ፣ ከዚህም አልፈው ሁለቱ ሥርዓቶች ማለትም የቀድሞይቱና አዲስቱ በመካከላቸው ጠላትነት እንዳይፈጥሩ በሰላም እርስ በራሳቸው እንዲተካኩ ጊዜን ይሰጣሉ። በዚህም አዲሲቲቱ ሥርዓት በቀድሞይቱ ላይ ቀስ በቀስ  እየበረታችና እየተተካች እንድትሄድ ያደርጋሉ። ይህንን መንገድ መከተል ለዘላቂ ዕድገትና መተማመን መሠረት ቢሆንም እስከ ሕይወት የሚያደርስ ትልቅ መስዋዕትነት ግን ሊያስከፍል እንዲችል አስቀድሞ ተረድቶ ሒደቱን በጥንቃቄ መመልከቱ መልካም ነው።  በ1953  የግርማሜዎቹን  ድንቆች ሕይወት ያስከፈለው እሳቤ ይኼኛው ነው።  

ሌላ ተጨማሪ የራስ ምታት  ሁላችንም እንደምንረዳው እንደ እኛ ባሉ አገር ላይ የሚከሰት ለውጥ አልጋ በአልጋ አይደለም፡፡ ለውጡን የሚመሩት መሪዎች ሳይቀር ስለለውጡ ፍርኃት እስኪያድርባቸው ድረስ የለውጡ ሒደት ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ሊያመራ ይችላል፣ የባቡሩም ሐዲድ መንገዱን ቢስት የሚከሰተውን ዓይነት ፍርኃት የሚያስፈራን ጉዞ መሪዎች መጓዛቸው የግድ ይሆንባቸዋል። እንደ እኛ ለ27 ዓመት በገዛ ወንድሞቹ ያለ ፈቃዱ ታፍኖ ያለ ሕዝብ ድንገት ሲለቀቅ ግራ መጋባቱ አይቀርም፣ ይህንንም ጉዞ የሚመራውም መሪም ማኅበረሰቡ የሚያደርገውን ምላሽ በእርግጠኝነት ለማወቅ ይቸገራሉ። ማኅበረሰቡ ድንገት ለውጥ ሲፈነጥቅለት ግራ ሊጋባ ይችላል፡፡ በዚህም ምክንያት የሚጠይቀው፣ የሚፈለገው፣ የሚመኝው ሁሉ የበዛ አንዱ ከሌላው ጋር የተመታታም ሊሆን ይሆናል። ከዚህም ሌላ እኛ ለውጥን ከጥይት ጩኸት ጋር ስለለመድናት፣ ሳይጥሉና ሳይወድቁ የተደረገ ለውጥ እኛ ዘንድ አልተለመደም። ከዚህ የተነሳም ለውጡን ወደለመድነው ተራ ኪሳራ ሊነዱ የሚወዱም አይጠፉም፡፡  የግራው የቀኙ  ፍላጎት፣ ሩጫ፣ ጫጫታ፣ ሁካታ ተደማምሮ ለውጡን አላስፈላጊ እንዲሆን፣ አይይይ ከዚህስ ይልቅ ሌላ ተጨማሪ 27 ዓመታትን ለመገዛት እንመርጣልን ብለን ጨዋታው ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ እንድንል ሒደቱ ይሞግተናል። ስለዚህ ጉዳይ  በሐርቫርድ የቢዝነስ ትምህርት ቤት መምህር የሆኑት ሮዛቤት ሞስ ካንተር እንዳሉት፣ ሁሉ ነገር መሃል ላይ ውድቀት ይመስላል። ስለሆነም ሒደቱን ዓይተንና ፈርተን ከሩጫችን ልንቆም አያስፈልግም።   

መሪዎች በሚገባ መንገዳቸውን የተረዱ ከሆነ በየመሃሉ የሚንገራገጨው የባቡር ፉርጎ አያስደነግጣቸውም። ስለሆነም መሪዎች መሥመራቸውን አጥብቀው በመረዳት እያንዳንዱን ሒደት አስቀድሞ በመረዳት፣ የተጠና መፍትሔ ለየችግሮቻቸው በአፋጣኝ በመስጠት፣ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን በማጠናከር፣ ችግር ፈቺና ኪሳራ አስተዳዳሪ ሥርዓትን በመዘረጋት ወደ ተነሱለት ትልማቸው ሊገሰግሱ ይገባል።

አንዲት አነስተኛ ጠጠር ከኩሬው ላይ ብትወረወር በኩሬው ላይ በሚፈጠረው ማዕበል የተነሳ የሚሠራው ክበባት እየሰፋ እየሰፋ ይሄዳል። እንዲት ትንሽ ጠጠር በመጠኗ ታይታ ተፅዕኖ ፈጣሪ እንዳይደለች በመገመት ችላ ልትባል አይገባም፡፡ ጠጠሪቷ መረበሽ የቻለችውን ያህል ተፅዕኖ ትፈጥራለች። እንደ እዚህች ዓይነት አነስተኛ ጠጠሮች ሲደመሩና ሲሰባሰቡ ግን ታላቅ ማዕበልን የመፍጠር ጉልበት ላይ መድረሷ አይቀሬ ነው። ስለሆነም እንደ አገሬ ሰው ሳይቃጠል እንዲሉ ነው ነገሩን በወጉ መመለከት መልካም ነው።

መሪዎች አንድ ችግር ተከስቶ፣ የክስተቱን ቁስል ለማከም ከመድከም ይልቅ ክስተቱ ቀድሞውኑ እንዳይከሰት ማድረግ ቢመርጡ ዘመናቸው የተረጋጋና ቀጣይ ይሆንላቸዋል። በሕክምና ሰዎች ዘንድ በሰፊው እንደሚታወቀው “Prevention is better than cure በመሆኑም አገር አቀፍ፣ ከተማ አቀፍ፣ መንደርና ጎጥ አቅድ ስልት አደረጃጀት፣ የመረጃ ቅብብሎሽ በማጠናከር በትንሹም፣ በትልቁም ሊከሰቱ የሚችሉን ቀውሶች ከእንጭጩ ሙሉ በሙሉ ማድረቅ ባይቻልም መቀነስ ግን ይቻላል።

ተንጠልጣይ ተስፋዎች መሪዎች በልጣን የመጀመሪያ ዘመናቸው በድል ስካር ውስጥ በመደወቃቸው ሳቢያ ይሁን አልያም ሆን ብለው የሰውን ቀልብ ለመውሰድ ይሁን ብቻ በሆነ አንዳች ሰበብ በርካታ ተስፋዎችን፣ ቅዶችን፣ ቃል ኪዳንህን እየማሉ ከማኅበረሰቡ ጆሮ ያንቆረቁራሉ ይኸው የመልካም ምኞታቸውና ሳባቸው ውሎ ሳያድር ግን በማበረሰቡ ዘንድ ቅሬታን ይፈጥርባቸዋል፡፡ ለመንገዳቸው ደንቃራ እንቅፋትም ሲሆን ይስተዋላል። ኅብረተሰቡ ምን ‘ፖለቲከ’ኞች ሲባሉ እኮ በመልክ ቢለያም እናታቸው አንድ ናትሁሉም ልጣናቸውን እስኪያደላድሉ ድረስ ሆዳችንን በተስፋ ነፈተው ነፍተው  ሆዳችን እንደተቀበተተ እንተኛለን፤ ከእንቅልፋችን ስንነቃ ባሮቻቸው አድርገውናል እንዳይል መታሰብ አለበት፡፡ ማኅበረሰባዊ መተማመንን ማግኘት ለለውጥ መሠረት ነው።

ልባም መሪዎች ተስፋ የሚሰጡትን ጉዳዮች ለይተው የተረዱ፣ ከራሳቸው መስመር ጋር ያስማሙና ያስተካከሉ ጠቢባን ናቸው። እኚህ መሪዎች ሊሩዋቸው የሚቻላቸውን ዋና ዋና ዕቅዶቻቸውን ለብረተሰቡ በመግለጽና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር በመግባት በማበረሰቡ ዘንድ ቅቡልነታቸውን እየጨመሩ፣ ማበረሰባዊ መተማመናቸውን እየገነቡ ይሄዳሉ እንጂ የማይፈጽሙ በርካታ አማላይ ቃላት በመደርደር ራሳቸውን ከማኀበረሰቡ ጋር በገዛ ምላሳቸው አይነጥሉም።

በመጨረሻም ለውጥ ሁሉንም እንደማያስደስት እርግጥ ነው። ስለሆነም የለውጥ ሐዋሪያት ሁሉንም ካላሰደሰትኩኝ ዘመቻ ውስጥ ራሳቸውን ከነከሩ ፍጹም ባድሎች ሊሆኑ አይችሉም። ይህ ማለት ግን አብዛኛውን ሰው ፍርኃት ውስጥ የሚከት፣ ከጥርጣሬና ከጭንቀት የሚዶል እንቅስቃሴ መሆን ግን የለበትም። መሪዎች ሁሉንም ባያደስቱም አብዛኛው ሰው ግን ሊቃወማቸው አያስፈልግም።  ምን አልባት አብዛኛው ማበረሰብ የሚቃወማቸው ጊዜ ሲገጥማቸው የነገሩን ምንጭ አንድ በአንድ በመመርመር፣ በመተንተንና በመረዳት ወደ ትክክለኛ መፍትሔና ውሳኔ በፍጥነት በመጓዝ ተቃዋሚዎቸውን ሳይቀር ደጋፊ ለማድረግ መንቀሳቀስ ይኖርባቸዋል ስለሆነም የባላንጣዎችን ተቃውሞና ጥያቄ መፍትሔ በመስጠት መጓዙ፣ በተቃዋሚው ጎራ ያለውን በርካታ ሕዝብ እያመነመነ ዝም ማስባል ብቻ ሳይሆን ደጋፊና አጋዥ የማድረጉን ዕድል የመፍጠር አቅም አለውና ተቃውሞን በቸልተኝነት መመለከት አያስፈልግም። ስለሆነም የዛሬዎቹን ተቃዋሚዎችና ባላንጣዎች ደጋፊና ወዳጅ ማድረግ እንጂ የዛሬዎቹን ደጋፊዎች የነገ ተቃዋሚዎች ማድረግ ከብልህ መሪዎች መንደር የሚጠበቅ አይደለም።

(ኢዮብ ክፍሉ ገብረሩፋኤል

ቨርጂኒያ፣ ሰሜን አሜሪካ)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...