- Advertisement -

‹‹ጥቅም ላይ ባልዋሉ የመሬት ይዞታዎች ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሁለተኛ ዙር በቅርቡ ይጀመራል›› ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ

በኢንቨስትመንትና በተለያዩ የልማት ሥራዎች ስም ተወስደው ለበርካታ ዓመታት ያለሙ የመሬት ይዞታዎችን ወደ ከተማ አስተዳደሩ የመሬት ባንክ የማስመለስ ዘመቻ ሁለተኛ ዙር በቅርቡ እንደሚጀመር፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

በምክትል ከንቲባነት የአዲስ አበባ ከተማን ማስተዳደር ከጀመሩ ሦስተኛ ወራቸው ላይ የሚገኙት ታከለ (ኢንጂነር)፣ በቆይታቸው ወቅት ከመሬት ጋር በተያያዘ የገጠማቸውን የተከማቸ ዝርክርክነት ‹‹ጉድ ነው›› ሲሉ ይገልጹታል፡፡

በልማት ስም ተወስደው በትንሹ አሥር ዓመትና ከዚያ በላይ ባለመልማታቸው የታጣውን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በቁጭት የተናገሩት ምክትል ከንቲባው፣ በመጀመርያው ዙር የመሬት ማስመለስ ተግባር ወደ አስተዳደሩ የመሬት ባንክ የተመለሰው መሬት ከ400 ሔክታር በላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ይኼንን ከአሥር ዓመት በላይ ሳይለማ ታጥሮ የተቀመጠ ይዞታን መጠን ሲገልጹትም፣ ‹‹አንድ መለስተኛ ከተማ›› እንደ ማለት ነው ብለዋል፡፡

ሁለተኛው ዙር ዘመቻ በቅርቡ እንደሚጀመርም ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት አጭር የስልክ ቆይታ አመልክተዋል፡፡

በሁለተኛው ዙር የሚካሄደው ያለሙ መሬቶችን የማስመለስ ዘመቻ በተለያዩ የልማት ዘርፎች የተወሰዱ ይዞታዎችን የሚመለከት ቢሆንም፣ በዋናነት ግን ለሪል ስቴት (የቤት ልማት) አልሚዎች ተላልፈው ለበርካታ ዓመታት ምንም ልማት ሳይካሄድባቸው ታጥረው ለተቀመጡ ይዞታዎች ምላሽ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

- Advertisement -

‹‹በጥቂት የሪል ስቴት አልሚዎች ብቻ ከመቶ ሔክታር በላይ የመሬት ይዞታ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ሳይሰጥ ተገኝቷል፤›› ያሉት ምክትል ከንቲባው፣ ይህ ዓይነቱ ሕገወጥነት እንደሚገታና የከተማዋ ነዋሪዎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች በፍጥነት ለሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ጥቅም ላይ እንደሚውሉ አስረድተዋል፡፡

በሪል ስቴት አልሚዎች ታጥረው ከተቀመጡ ይዞታዎች በተጨማሪ፣ በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ካባዎች (የድንጋይ ማምረቻ ይዞታዎች) ጉዳይም በሁለተኛው ዙር ዘመቻ ምላሽ እንደሚያገኝ ተናግረዋል፡፡

እሳቸው እንደሚሉት የከተማዋ ወጣቶች ሥራ አጥተው በተቀመጡበት ሁኔታና ይህ ችግርም የከተማዋ ራስ ምታት ሆኖ ሳለ፣ የድንጋይ ማምረቻ ይዞታዎችን በባለቤትነት ለበርካታ ዓመታት በብቸኝነት ይዞ ጥቅም ማጋበስ ኢፍትሐዊነት ስለሆነ ማስተካከያ እንደሚደረግበት ጠቁመዋል፡፡

‹‹የአንዳንዶቹ ካባዎች (ኳሪዎች) ባለቤቶች በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች ናቸው፤›› ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) ሰሞኑን የወሰዱት ዕርምጃ በሦስት ከንቲባዎች ያልተደፈረ በአገሪቱ የፖለቲካ ማዕከል ከለላ የተሰጣቸው ይዞታዎች መሆናቸው ይታወቃል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...

የኢትዮጵያ ጂዲፒ በውጭ ምንዛሪ ለውጡ ምክንያት ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር መውረዱ ተገለጸ

የአገሪቱ የውጭ ዕዳ ጂዲፒ ጥምርታ ለደሃ አገሮች ከተቀመጠው ጣሪያ አልፏል የኢትዮጵያ ኖሚናል ጂዲፒ (የዋጋ ንረትን ታሳቢ ያላደረገ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት) በዶላር ሲተመን፣ በሰኔ ወር...

ከአፋር በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለተፈናቀሉ ተጨማሪ ድጋፍ ተጠየቀ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች በሙሉ ተፈናቅለዋል ተብሏል በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን በሚገኙት በአዋሽ ፈንታሌና በዱለቻ ወረዳዎች በቀጠለው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከአካባቢው ለተፈናቀሉ ዜጎች እየቀረበ ያለው...

በውዝግብ የተሞላው 18ኛው የአዲስ አበባ የንግድ ዘርፍ ማኅበራት ጉባዔና ምርጫ እያነጋገረ ነው

ከጉባዔው አንድ ቀን በፊት አባል ሆነው የተመረጡ 55 ነጋዴዎች ለቦርድ አባልነት መቅረባቸውም ግርምትን ፈጥሯል የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት መተዳደሪያ ደንብ፣ ጠቅላላ ጉባዔው...

የአየር ንብረት ለውጥ በግብርናው ዘርፍና አመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጫና በኢትዮጵያ ግብርናና የአመጋገብ ሥርዓት ላይ አደጋ ደቅኗል ተባለ፡፡ ይህ የተነገረው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብና...

በምርጫ ወቅት ማጭበርበር አምስት ዓመታት እንደሚያስቀጣ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011ን ለመተካት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተረቀቀው አዲስ አዋጅ፣ በተጭበረበረ መረጃ ለመወዳደርና ለመመረጥ የሚሞክሩ...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን