‹‹ሰጥቶ መቀበል ለመረዳት የምሁራንን ትርጉም መጥቀስ አልፈልግም፡፡ በቀላሉ ለማስቀመጥ የሚሰጠው ያለውና የሚቀበለውን የሚፈልግ ሁለት ወገኖች የሚደራደሩበት አሠራር ነው፡፡ ሥልጣኑን የጠቀለሉት ወገኖች የአገሪቱን የፖለቲካ ቁልፎች ይዘዋል፤ አሁን ሕዝቡ ስለሚፈልገው መስጠት አለባቸው፡፡ ድሮም ተቀምቶ እንጂ የራሱ የሕዝብ ነበር፡፡›› የሚል ኃይለ ቃል በመቅደሙ ላይ ያሠፈረው መጽሐፍ ‹‹የችግራችን መፍትሔ እስከ ሰጥቶ መቀበል›› ይሰኛል፡፡ በወንድምስሻ አየለ የተዘጋጀው መጽሐፍ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ማኅበረ ፖለቲካ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው፡፡
መጽሐፉ የፖለቲካ ሥርዓቱ የሚታዩበትን ሕፀፆች ነቅሶ ከማውጣት ባሻገር ከጥንታውያን መንግሥት አንስቶ በተለይም ከ19ኛው እስከ 21ኛው ምዕት ድረስ አገሪቱን የመሩ ነገሥታትና መሪዎችንም ‹‹ኑ እናመስግን. . . ›› በሚል አዎንታዊ ተግባራቸውን አጉልቷል፡፡
መጽሐፉ በሦስት ክፍሎች በ13 ምዕራፎች የተደራጀ ሲሆን ዋጋውም 50 ብር ነው፡፡