- Advertisement -

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአውሮፓ ከሚኖሩ ከ20 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ይወያያሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ሥልጣን ከመጡ ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ በሚያደርጉት የአውሮፓ ጉበኝት ከ20 እስከ 25 ሺሕ የሚጠጉ በአውሮፓ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር በጀርመን ፍራንክፈርት እንደሚገናኙና ንግግር እንደሚያደርጉ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየ15 ቀኑ በሚሰጠው መግለጫው አስታወቀ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ያስታወቀው ሐሙስ ጥቅምት 8 ቀን 2011 ዓ.ም. በቃል አቀባዩ መለስ ዓለም አማካይነት፣ በጉብኝቱና ባለፉት 15 ቀናት በተከናወኑ ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ አውሮፓ የሚያቀኑት ወደ ፈረንሣይና ጀርመን ሲሆን፣ ጉብኝቱም የፈረንሣይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮንና የጀርመኗ መራሒተ መንግሥት አንገላ መርከል ባደረጉላቸው ግብዣ መሠረት መሆኑን ቃል አቀባዩ አስረድተዋል፡፡

ለአንድ ሳምንት ያህል በሚዘልቀው ጉብኝት ጠቅላይ ሚኒስትሩ   ከሁለቱ መሪዎች ጋር በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊና እንዲሁም በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ቃል አቀባዩ አክለው አስረድተዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ ‹‹አንድ ሆነን እንነሳ ነገን እንገንባ›› በሚል መሪ ቃል፣ በመላው አውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ንግግር እንደሚያደርጉም ይጠበቃል፡፡

ፍራንክፈርት አዘጋጅ እንድትሆን የተመረጠችበትን ምክንያት ያብራሩት ቃል አቀባዩ፣ ‹‹የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውሮፓ ጉዞ የመጨረሻ ጉዞ ጀርመን በመሆኑና በአንፃራዊነትም በርካታ ቁጥሮች ያላቸው ኢትዮጵያውያን ስለሚኖሩ፣ እንዲሁም ለብዙዎቹ ኤምባሲዎቻችን አማካይ ቦታ ላይ ስለሚገኝ ነው፤› ብለዋል፡፡  

- Advertisement -

ከተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የሚወከሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአገሪቱ መጪው ዕድል፣ የመንግሥት ዕቅድና ክንውንና አሁን በተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ በሚኖራቸው አስተዋጽኦ ላይ ጥያቄያቸውን፣ ፍላጎታቸውንና ራዕያቸውን እንደሚያቀርቡና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሐሳብ የሚለዋወጡበት ዕድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ሥልጣን የያዙ ሰሞን ወጪ ለመቀነስ በማሰብ፣ ሚኒስትሮች የውጭ አገር ጉዟቸውን እንዲቀንሱ ወይም እንዲሰርዙ መመርያ መስጠታቸው ይታወሳል፡፡ የእሳቸው ጉብኝት ከዚህ መርህ አንፃር እንዴት ይታያል? ተብሎ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ቃል አቀባዩ፣ ‹‹ወጪ መታሰብ አለበት፡፡ የታክስ ከፋይ ኅብረተሰብ ሀብት አላስፈላጊ በሆነ መንገድ መውጣት የለበትም፡፡ ይህ ማለት ግን ከሌሎች አገሮች ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አታደርግም ወይም ትመንናለህ ማለት አይደለም፤›› ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

‹‹የተመረጡ ሥራዎች ይሠራሉ፡፡ በተለይም የውጭ ግንኙነት ዘርፍ ባህሪው ሆኖ እየተጓጓዝክ የምትሠራው ሥራ ነው፡፡ ሌሎች የሚመጡትን ያህል ስትጋበዝም መሄድ ያስፈልጋል፡፡ ከዚያ ጋር የሚጣረስ ነገር የለውም፡፡ ውስን ሀብታችን ግን በጥንቃቄ መጠቀም አለብን፡፡ ይኼ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ቋሚ መርህ ነው፤›› በማለት አብራርተዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

በተያዘው ወር መጨረሻ  አዲስ ፖስፖርትና ቪዛ  ይፋ ይደረጋል ተባለ

በውጭ አገር የሚታተመውን ፓስፖርትና አገሪቱ ለውጭ ዜጎች የምትሰጠውን ቪዛ በአዲስ ይዘትና ኅትመት በአገር ውስጥ ታትሞ በተያዘው ወር የካቲት 2017 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽንና ዜግነት...

በውጭ አገር ለሚሰጥ ሕክምና የአገር ውስጥ ተወካይ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚያስገድድ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

የጤና ሚኒስቴርን ፈቃድ አግኝተው በውጭ አገሮች የሕክምና አገልግሎት ተቋማት የሚታከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የሕክምና አገልግሎት ጥራት ደረጃ ጉድለት፣ የሕክምና ስህተት ወይም የሙያ ግድፈት ቢፈጸምባቸው፣ የውጭ ሕክምና...

በአማራ ክልል የአሽከርካሪዎች ዕገታን መደበኛ የሥራ ቦታ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው መበራከቱ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የአሽከርካሪዎች ዕገታ በአሁኑ ወቅት ክፍት የሥራ ቦታ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ፡፡ አሽከርካሪዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና ሲያዙም በአግባቡ በሕግ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ከተወዳዳሪው ኩባንያ ቅሬታ እየቀረበበት መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያ ቴሌኮም ጉልህ የገበያ ድርሻ እያለው አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ለተወዳዳሪው ኩባንያው ውድድሩን አስቸጋሪ ስላደረገበት፣ ‹‹መንግሥታዊ ኩባንያው ዋጋ እንዲጨምር መገደድ አለበት የሚል የቅሬታ ጥያቁ...

በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት 39 ምድብ ችሎቶች ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸው ተረጋገጠ

በስድስት ወራት 89 ዳኞች ሥራ መልቀቃቸው ተነግሯል የክልሉ ዳኞች ያለመከሰስ መብት ተጠበቀላቸው በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት ከ221 ፍርድ ቤቶች 39 የዞንና የወረዳ ምድብ ችሎቶች አገልግሎት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን