Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየኢትዮጵያና ኤርትራ ውጥረት እንዳይባባስ ተሰግቷል

የኢትዮጵያና ኤርትራ ውጥረት እንዳይባባስ ተሰግቷል

ቀን:

የኢትዮጵያና የኤርትራ ግጭት እንዳይባባስና ወደ ጠቅላላ ጦርነት እንዳይሸጋገር ተሰግቷል፡፡ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ሁለቱም አገሮች አለመግባባታቸውን በድርድር እንዲፈቱ ጥሪ እያቀረበ ይገኛል፡፡

በድንበር ውዝግብ የተነሳ በ1990 ዓ.ም. ወደ ሙሉ ጦርነት የገቡት ሁለቱም ጎረቤት አገሮች፤ ከ16 ዓመታት በኋላ እንደገና ወደ ጠቅላላ ጦርነት እንዳይገቡ በብዙዎች ተሰግቷል፡፡ አሜሪካና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሁለቱም አገሮች ከጦርነት እንዲታቀቡ አሳስበዋል፡፡

በአገሮቹ መካከል የቆየው ሰላምም ጦርነትም አልባ ሁኔታ ባለፈው እሑድ የተቀየረ ሲሆን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በፆረና ድንበር አካባቢ በሁለቱም አገሮች መከላከያ ኃይሎች መካከል መደበኛ የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል፡፡

አንዳንድ የሪፖርተር ምንጮች እንደሚሉት፣ ከግጭቱ በኋላ የኤርትራ መከላከያ ኃይል አንዳንድ ስትራቴጂካዊ ምሽጎችን ለቆ ወደ ኋላ ያፈገፈገ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ወታደሮች ከሁለቱም ወገኖች መገደላቸው ታውቋል፡፡

ግጭቱን በትክክል ማን እንደጀመረው እስካሁን በገለልተኛ ወገን ያልተረጋገጠ ሲሆን፣ ሁለቱም አገሮች እርስ በርስ በመወነጃጀል ላይ ይገኛሉ፡፡

ቢቢሲ እንደዘገበው፣ የኤርትራ መንግሥት ከኢትዮጵያ ለተሰነዘረበት ጥቃት ሲከላከል ሁለት መቶ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል አባላት ተገድለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በግጭቱ ስለደረሰው ጉዳት እስካሁን ባይገልጽም፣ መከላከያ ኃይሉ አስፈላጊውን የአጸፋ ምላሽ አድርሶ ወደ ቀድሞ ቦታው መመለሱን ይናገራል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ግጭቱ መቋረጡ ይፋ ቢያደርግም ምንጮች እንደሚሉት ቡሬንና ፆረና ጨምሮ በተለያዩ የድንበር ግንባሮች ውጥረት መንገሱና ከባድ የጦር መሳሪያ ልውውጥ መሰማቱን ቀጥሏል፡፡

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያና ኤርትራ የድንበር ግጭት እንዳይባባስ ሥጋት ያደረበት ሲሆን፣ በተለይ ተመድና የአሜሪካ መንግሥት ሁለቱም አገሮች ወደ ከፋ ጦርነት ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስበዋል፡፡

የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪሙን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝን በብራስልስ አግኝተው፤ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ያለው ችግር በድርድርና በሰላም እንዲፈቱ ጥያቄ ማቅረባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩሉ ባወጣው መግለጫ ሁኔታው እጅግ እንዳሳሰበውና ሁለቱም አገሮች ቀደም ሲል የፈረሙትን የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያከብሩ አሳስቧል፡፡

ኢትዮጵያና ኤርትራ በ1990 ዓ.ም. በድንበር ሳቢያ ወደ ሙሉ ጦርነት የገቡ ሲሆን፣ ድንበር ኮሚሽኑ የሰጠው ውሳኔ በኢትዮጵያ ተቀባይነት አላገኘም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...