Sunday, September 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የ288 ባለሀብቶችን የመሬት ጥያቄ አገደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የ288 ባለሀብቶችን የመሬት ጥያቄ አገደ

ቀን:

 

 

ቅዳሜ ጥቅምት 17 ቀን 2011 ዓ.ም. የተሰበሰበው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ፣ 288 ባለሀብቶች ለፋብሪካ ግንባታ ያቀረቡት የመሬት ጥያቄ እንዳይስተናገድ አገደ፡፡

ባለሀብቶች በተናጠል ለሚያካሂዷቸው የማኑፋክቸሪንግ ግንባታ በአጠቃላይ 133.65 ሔክታር መሬት እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበው፣ አስተዳደሩ የጠየቁትን መሬት እንደሚሰጣቸው በማመን ሲጠባበቁ ነበር፡፡

የተፋለሱ አሠራሮችን በማስተካከል ሥራ ላይ የተጠመደው በምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) የሚመራው ካቢኔ፣ የባለሀብቶቹን የመሬት ጥያቄ ባህሪያት ከመረመረ በኋላ ጥያቄያቸው እንዳይስተናገድ ዕግድ አስተላልፏል፡፡

መረጃዎች እንደጠቆሙት ካቢኔው ያሳለፈው እግድ በሁለት ጉዳዮች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የመጀመሪያው ከዚህ ቀደም ለአልሚዎች መሬት ሲተላለፍ የቆየው ግልጽነት በጎደለው መንገድ ነው፡፡

‹‹የከተማውን የወደፊት ራዕይ ከግምት ያላስገባ፣ ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የወጣውን መመርያ ቁጥር 16/2005 ያልተከተለ ብሎም ያፋለሰ ነው፤›› በማለት ካቢኔው፣ ቀደም ሲል መሬት የተሰጠበት አሠራር በጥልቀት እንዲታይና አዲስ የቀረቡት  ጥያቄዎችም እንዳይስተናገዱ ዕግድ ጥሏል፡፡

ሁለተኛው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተናጠል የኢንዱስትሪ ልማት መሬት ጥያቄ መቀበል በማቆም፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማልማት የባለሀብቶችን ጥያቄ ለማስተናገድ ውሳኔ በማሳለፉ ነው፡፡

በዚህ መሠረት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ፣ የአነስተኛና የመካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ኮርፖሬሽን የተሰኘ ተቋም አቋቁሟል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ጊዜ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 93.9 ሔክታር መሬት ተረክቦ የኢንዱስትሪ ዞን ለመገንባት የተለያዩ ጥናቶችን እያካሄደ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢንዱስትሪ በከለላቸው ቦታዎች በርካታ ባለሀብቶች መሬት ወስደዋል፡፡ ከ2004 ዓ.ም. እስከ 2010 ዓ.ም. ድረስ 495.3 ሔክታር መሬት ለባለሀብቶች መተላለፉ ተገልጿል፡፡

ነገር ግን በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ጥናቶች እነዚህ ቦታዎች ለታለመላቸው ግንባታዎች አልዋሉም፡፡ አብዛኞቹ ከውል ውጪ ለሆኑ ግንባታዎች ከመዋላቸው በተጨማሪ፣ ግንባታ ሳይካሄድባቸው የሚገኙ ሰፋፊ ቦታዎች መኖራቸውም ተመልክቷል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...