Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅየአረጋውያኑ መድረክ

የአረጋውያኑ መድረክ

ቀን:

‹‹ቀደምት የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾችን በመዘከር የኢትዮጵያ አረጋውያንን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት እናረጋግጥ›› በሚል መሪ ቃል የተከበረው የዘንድሮ የዓለም አረጋውያን ቀን የማጠቃለያ ሥነ ሥርዓት ጥቅምት 28 ቀን 2011 ዓ.ም. በሚሌኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አረጋውያን በተገኙበት መድረክ የኢትዮጵያ አረጋውያን ማኅበር ፕሬዚዳንት አባ ሙዳ አበበ ኃይሉ ባሰሙት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ከስድስት ሚሊዮን በላይ አረጋውያን መካከል አብዛኞቹ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ችግሮች አሉባቸው ብለዋል፡፡  ማኅበሩ የአረጋውያንን መብትና ጥቅም ለማስከበር እየሠራ መሆኑንና መንግሥትም ለዚሁ ተግባር ድጋፉን እንዲያጠናክር ጥያቄ አቅርበዋል። በሥነሥርዓቱ የተገኙት የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ባሰሙት ዲስኩርም፣ መንግሥት ባለውለታዎቹን አረጋውያን በእርጅና ዘመናቸው የሚደርሱባቸውን ችግሮች ለማቃለል  ቀጣይነት ያላቸውን ተግባራት በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል። አያይዘውም በተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ የጥፋት ድርጊቶችን ለማረም አረጋውያን ዕውቀትና ጥበባቸውን ተጠቅመው ለዘላቂ ሰላም መስፈን እንዲሠሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ፎቶዎቹ የመድረኩን ከፊል ገጽታ ያሳያሉ፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...