Friday, September 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናፓርላማው የቋሚ ኮሚቴ ዕጩዎችን በከፍተኛ ተቃውሞ ውድቅ አደረገ

ፓርላማው የቋሚ ኮሚቴ ዕጩዎችን በከፍተኛ ተቃውሞ ውድቅ አደረገ

ቀን:

ፓርላማው ዛሬ ጥቅምት 30 ቀን 2011 .. ባደረገው ልዩ ስብሰባ፣ አዲስ ለተቋቋሙት አሥር ቋሚ ኮሚቴዎች ያቀረባቸውን ሁለት ዕጩዎች በከፍተኛ ድምፅ ውድቅ አደረገ፡፡

ፓርላማው ማክሰኞ ጥቅምት 27 ቀን 2011 .. ባደረገው ስብሰባ የቋሚ ኮሚቴ አደረጃጀቱን ሃያ ወደ አሥር ዝቅ እንዲል አድርጎ ካፀደቀ በኋላ፣ በሰብሳቢዎቹ ላይ ሳይስማማ መቅረቱ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ በነበረው ስብሰባ ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበባቸው አቶ ሞቱማ መቃሳና አቶ አማኑኤል አብርሃም ሲሆኑ፣ አቶ አማኑኤል ከዕጩነት ራሳቸውን አግልለው ነበር፡፡

ይሁንና ዛሬ በተካሄደው ስብሰባ ምክር ቤቱ አቶ ሞቱማ መቃሳን 152 ድምፅ ውድቅ ያደረገ ሲሆን፣ አቶ አፅበሀ አረጋዊን ደግሞ 157 ድምፅ ውድቅ አድርጓል፡፡

የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ሞቱማ መቃሳ በዕጩነት የቀረቡት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴን እንዲመሩ ነበር፡፡ አቶ አፅበሀ ደግሞ የገቢዎች፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴን እንዲመሩ ነበር የታጩት፡፡

በዛሬው ዕለት በተካሄደው ስብሰባ ራሳቸውን ባገለሉት አቶ አማኑኤል ምትክ / ፎዚያ አሚን ለሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ታጭተው በአብላጫ ድምፅ አልፈዋል፡፡ቀሪዎቹ ቋሚ ኮሚቴዎች ሰብሳቢነት የቀረቡ ዕጩዎች በሙሉ ድምፅ አልፈዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...