Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላ ወዳጃቸው ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ጋዜጠኛ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዴት ነህ?
  • እናንተማ ግራ ተጋብታችሁ እኛንም ግራ ታጋቡናላችሁ አይደል?
  • እንዴት?
  • ባለፈው የተሠራውን አላዩም እንዴ?
  • ምን ተሠራ?
  • እኛ ግን የእንጀራ ልጆች ነን ማለት ነው?
  • ምንድነው የምታወራው?
  • ለውጥ ላይ ነን አላላችሁም?
  • ለእሱማ ጥርጥር የለውም፡፡
  • ታዲያ ለውጡ ሁሉን አቀፍ ነው አልተባለም?
  • በትክክል እንጂ፡፡
  • ለምንድነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቋቋሙት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ላይ ያልተጠራነው?
  • ያልተጠራችሁበት ምክንያት አለ፡፡
  • የእንጀራ ልጆች ስለሆንን ነው?
  • ባይሆን የእንጀራ ጋዜጠኞች ስለሆናችሁ ሊሆን ይችላል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በርካታ የሚዲያ ተቋማት ቅር ተሰኝተዋል፡፡
  • ለምንድነው ቅር የሚሰኙት?
  • እየተገለልን ነው ብለው ነዋ፡፡
  • ስማ ሚዲያዎቹ የተመረጡት እኮ የተቀመጠላቸውን መሥፈርት ያሟሉት ብቻ ናቸው፡፡
  • መሥፈርቱ ትክክል አይደለማ?
  • ታዲያ በየሥርቻው ሚዲያ እያቋቋማችሁ ሁሉም ይጠራ ቢባል እንዴት ይሆናል?
  • እንደ እሱ እያልኩ አይደለም፡፡
  • ለመሆኑ አንተ የት ነው ምትሠራው?
  • እኔማ በየኢንተርኔቱ ምናምን እጽፋለሁ፡፡
  • ስለዚህ እንደ አንተ ዓይነቱ ተጠርቶ ፕሬስ ኮንፈረንሱ ስታዲዮም ይደረግ?
  • ምን ማለት ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • በአሁኑ ወቅት ሲቲዝን ጆርናሊዝም እያላችሁ ሁሉም ሰው እንደ ጋዜጠኛ ያደርገዋል አይደል?
  • እነሱ ይጠሩ ማለቴ አይደለም፡፡
  • ስለዚህ አሁን የተወሰነው ውሳኔ ትክክል ነው ባይ ነኝ፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • በቃ ዜና ሲጨርስ ሙዚቃ የሚያሳይ ጣቢያ የተምታታበት ስለሆነ እንዲህ ዓይነቱ ትልቅ ቦታ ባይጠራ አይገርመኝም፡፡
  • እ . . .
  • አንዳንዶች ደግሞ ሰርቆ አደሮች ናቸው፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • የራሳቸው ዘገባ አይሠሩም፣ ዝም ብለው የሌሎቹን ሚዲያዎች ሥራ የራሳቸው አስመስለው ነው የሚለጥፉት፡፡
  • እሱስ ልክ ነዎት፡፡
  • ስለዚህ ሚዲያዎቹ የተመረጡበት መንገድ ትክክል ነው ባይ ነኝ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ሚዲያ እኮ የሕዝብ ድምፅ ነው፡፡
  • የተመረጡት እኮ የሕዝብ ድምፅ የሆኑት ናቸው፡፡
  • ግን በርካቶች ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው፡፡
  • እሱ መብታቸው ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከእርስዎ ጋር ጥሩ ወዳጅነት ነው ያለን፡፡
  • ታዲያ ምን ላድርግልህ?
  • የተለያዩ ሚዲያዎች ወክለውኝ ነው የመጣሁት፡፡
  • ለምንድነው የተወከልከው?
  • እነዚህ ሚዲያዎች መካተት ይፈልጋሉ፡፡
  • ታዲያ ምን ልርዳህ?
  • በእርስዎ በኩል ጉዳዩን እንዲጨርሱት ነዋ፡፡
  • ለእኔ ጉዳዩን መጨረስ ቀላል ነው፡፡
  • አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔም ግን ከእናንተ የምጠብቀው ነገር አለ፡፡
  • ምንድን?
  • ኮሚሽን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላ ወዳጃቸው ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ሰሞኑን ተዳከምን አይደል ክቡር ሚኒስትር?
  • በምኑ?
  • በቃ የቢዝነስ ሐሳብም እያመጣን አይደለም፡፡
  • የእኔ ጭንቅላት ቀን ከሌት አርፎ አያውቅም፡፡
  • ግን ምን ሐሳብ አለዎት?
  • ሰሞኑን ቲቪ ሳይ የመጣልኝ ሐሳብ አለ፡፡
  • ንገሩኛ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ከፍተኛ አመራሮቹን አላየሃቸውም?
  • ምን ሆኑ?
  • አለባበሳቸውን ተመልክተኸዋል?
  • ያው ዘናጮች ናቸው፡፡
  • እሱማ ይታወቃል፡፡
  • ታዲያ አለባበሳቸው ሌላ ምን አለው?
  • አላስተዋልከውም እንጂ በዓመት አንዴ የሚከበረው በዓል በየሳምንቱ እየተከበረ ነው፡፡
  • የምን በዓል ነው?
  • የብሔር ብሔረሰቦች በዓል ነዋ፡፡
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር?
  • በአንዱ ሳምንት የሰሜን ሸዋ በርኖስ ይለበሳል፣ ሌላው ሳምንት የራያ ባህላዊ ልብስ ይለበሳል፡፡
  • ልክ ነዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሌላው ደግሞ የአክሱም ጽዮን የጵጵስና ልብስ ሲለብስ፣ ሌላው ደግሞ የአባ ገዳን ልብስ ይለብሳል፡፡
  • ጥሩ ያስተውላሉ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አየህ በፊት እነዚህ ልብሶችን የሚያስተዋውቁት ሞዴሎች ነበሩ፣ አሁን ግን ፖለቲከኞቻችን ጥሩ ሞዴሎች ሆነውልናል፡፡
  • ሐሳብዎት እኮ ሁሌ ያስገርመኛል፡፡   
  • ስለዚህ አሁን ቢዝነሱ የአልባሳት ነው፡፡
  • እሱማ ጋርመንት ላይ አተኮሮ የሚሠራ ኢንዱስትሪያል ፓርክ አለን አይደል እንዴ?
  • ስለዚህ ቀጣዩ አዋጭ የቢዝነስ ዘርፍ እሱ ነው፡፡
  • ታዲያ ምን እያሉኝ ነው?
  • ከአንድ አንድ የምንገባበት ቢዝነስ እሱ ነው፡፡
  • ምን?
  • ሽመና!

[ክቡር ሚኒስትር ዳያስፖራ ወዳጃቸው ጋ ይደውላሉ]

  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዴት ነህ ወዳጄ?
  • ምን እያደረጋችሁ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን አደረግን?
  • ያን ሁሉ ዲስኩር የት አደረሳችሁት?
  • የምን ዲስኩር ነው?
  • አገር ሰላም ነው አገራችሁ ግቡ ምናምን ያላችሁትን ነዋ፡፡
  • አሁንም ጥሪ እያቀረብን እኮ ነው፡፡
  • ምን ነካዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ምነው?
  • ዳስፖራው እኮ ጥሪውን አክብሮ መጥቶ ነበር፡፡
  • ታዲያ ምን አጎደልን?
  • አሁንም ሁሉም ተመልሶ እየወጣ ነው፡፡
  • ለምን?
  • ዲስኩር ወዲያ ሪያሊቲ ወዲህ ሆነበታ?
  • አልገባኝም?
  • በየዕለቱ የሚሰማው ወሬ አስፈሪ እኮ ነው፡፡
  • የምን ወሬ ነው?
  • አገሪቱ በየዕለቱ እየተሸነሸነች እኮ ነው፡፡
  • ማን ነው የሚሸነሽናት?
  • ክቡር ሚኒስትር ከአንድነት ይልቅ ልዩነት ላይ እያተኮርን ክልልነት በወረዳ ደረጃ መውረዱ አይቀርም፡፡
  • እ . . .
  • በየቦታው የሚሰማው ግጭት እኮ አስፈሪ ነው፡፡
  • ለውጥ ሲኖር ግጭት ያለ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የእኔ ፍራቻ ሌላ ነው፡፡
  • ምንድነው ፍራቻህ?
  • ከለውጡ ያተረፍነው ግጭት ብቻ እንዳይሆን?
  • እ . . .
  • ክቡር ሚኒስትር እንደ ዩጎዝላቪያ እንዳንሆን ነው ፍራቻዬ፡፡
  • ኧረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ዜጎች እኮ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ሀብት ማፍራትና መኖር አልቻሉም፡፡
  • እሱማ ልክ ነው፡፡
  • በየቦታው እኮ መሣሪያ ተያዘ፣ ቦምብ ፈነዳ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡
  • ስማ ይኼ እኮ በፊትም የነበረ ነው፡፡
  • ታዲያ እንዴት አንሰማም ነበር?
  • አሁን ሚዲያውን ስለከፋፍትነው ነው ወሬው ሁሉ ቶሎ የሚሰማው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ችግሩ አሳሳቢ ነው፡፡
  • ስነግርህ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ ይፈታል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ፋብሪካዎች እየተዘጉ ነው እኮ፡፡
  • እ . . .
  • ይኼው ሠራተኞቻቸውን እየቀነሱ እኮ ነው፡፡
  • እሱንማ አውቃለሁ፡፡
  • ኢኮኖሚውም አሥጊ ሁኔታ ላይ ነው ያለው፡፡
  • አንተ ግን ለምን ቀና ቀናውን አታስብም? ምን አሁን እናንተም አገር እንደዚሁ ዓይነት ችግር አለ አይደል?
  • ክቡር ሚኒስትር ኢትዮጵያ ያለው ግን በጣም ትኩረት የሚሻ ነው፡፡
  • ለማንኛውም ዛሬ የደወልኩልህ ለአንድ ጉዳይ ነው፡፡
  • ምን ፈለጉ ክቡር ሚኒስትር?
  • ያው ገንዘብ እንድታስቀምጥልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ለምንድነው ገንዘብ አሜሪካ የሚያስቀምጡት?
  • ምን ችግር አለው?
  • ማለቴ ኢትዮጵያ ሰላም ነው ምናምን እያሉኝ አይደል እንዴ?
  • ያው ለሕክምና ምናምን ካስፈለገኝ ብዬ እንጂ አብዛኛው ንብረቴ እኮ እዚህ ነው ያለው፡፡
  • እንደዚያ ከሆነ እኮ በጣም ሀብታም ነዎት ማለት ነው፡፡
  • እንዴት?
  • አብዛኛውን ንብረትዎ ኢትዮጵያ ካለ በእኔ በኩል የላኩት ገንዘብ ራሱ የትየለሌ ነው እኮ፡፡
  • እሱስ ሁሉም ሀብቱን ስለሚደብቅ ነው፡፡
  • ታዲያ መቼ ነው የሚልኩት?
  • እኔማ አሁኑኑ መላክ እችላለሁ፡፡
  • በቃ ይላኩት፡፡
  • ዋጋው እንደተለመደው ነው አይደል?
  • ክቡር ሚኒስትር ትንሽ ጨምሯል፡፡
  • ለምን?
  • በቃ በሙስና ዘመቻው ምክንያት ሁሉም ሀብቱን እያሸሸ ስለሆነ ተመኑ ተቀይሯል፡፡
  • ታዲያ በስንት ነው የምትቀይርልኝ?
  • በ40!

[ክቡር ሚኒስትሩ ልጅ አስቸግሮ ትምህርት ቤት ተጠርጠው ከዳይሬክተሩ ጋር እያወሩ ነው]

  • በጣም የሥራ ውጥረት እንዳለብኝ አታውቁም?
  • እናውቃልን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ታዲያ ለምንድነው የምትጠሩኝ?
  • ከምንም በላይ የልጅዎ ጉዳይ ያሳስብዎታል ብለን ነው፡፡
  • እናቱ ነበር የምትመጣው አሁን ለጊዜው አገር ውስጥ ስለሌለች ነው፡፡
  • ስላስቸገርንዎ እንግዲህ ይቅርታ፡፡
  • በነገራችን ላይ ይኼን ሁሉ ገንዘብ እያስከፈላችሁን የረባ እንኳን መጫወቻ የላችሁም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እሱን ሌላ ጊዜ እናወራለን፡፡
  • እንዴ ለመሆኑ ልጆቹ ምሳቸውን የት ነው የሚበሉት? ምንም ዓይነት ሼድ አላየሁም?
  • የመጡት እኮ እሱን እንድናወራ አይደለም፡፡
  • በዚያ ላይ በቂ የመኪና መቆሚያ እንኳን የላችሁም፡፡
  • ምን ሆኑ ክቡር ሚኒስትር?
  • መናገር ስላለብኝ ነው፣ ጥበቃዎቹ እኮ በጣም ሽማግሌዎች ናቸው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከመጡበት አጀንዳ በጣም ዳይቨርት ያደረገ ነገር ነው የሚያወሩት፡፡
  • ልጄ እንደዚህ ዓይነት ትምህርት ቤት መማሩ ያሳስበኛላ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኛ ደግሞ ልጅዎ ለትምህርት ቤታችን ሥጋት ስለሆነ ልናባርረው ነው፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ተማሪዎቹን ሱስ በማስለመድ፣ ክፍል ውስጥ ከፍተኛ ረብሻና ሁከት በማስነሳት የትምህርት ሥርዓቱን እያስተጓጎለ ነው፡፡
  • አልገባኝም?
  • ትምህርት ቤቱ ውስጥ የግሩፕ ፀብ በመቀስቀስ ለተማሪዎች ከፍተኛ ሥጋት ሆኗል፡፡
  • የእኔ ልጅ ነው እንደዚህ የሚያደርገው?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ የምለው ተማሪዎች ጥበብ የሚያገኙት እኮ ከትምህርት ቤት ነው፡፡
  • አውቃለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የተማሪዎች የሥልጣኔ መገለጫም ትምህርት ቤት ነው፡፡
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የትምህርት ቤታችሁ ችግር ሲቀረፍ የእኔም ልጅ ችግር ይቀረፋል፡፡
  • አሁን አንድ ተረት አስታወሱኝ፡፡
  • ምን የሚል ተረት?
  • የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች!  

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...