Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ወዳጃቸው ጋር ተገናኙ

[የክቡር ሚኒስትሩ ወዳጅ ሊያገኛቸው ቤታቸው ይሄዳል]

  • ክቡር ሚኒስትር በሰላም ነው?
  • በሰላም ነው ስትል?
  • እልም ብለው ጠፍተዋል፡፡
  • ምን ላድርግ ብለህ ነው?
  • እኔ እኮ እርስዎን ለማግኘት እንደ ጠበል ቀማሽ በየድግሱ አልጠፋም፡፡
  • አልገባኝም?
  • በቃ ኤምባሲ ቢሉ መንግሥት፣ ከዚያም አልፎ የከተማችን ሀብታችሞ በሚደግሱት ድግስ እርስዎን ለማግኘት ቀርቼ አላውቅም፡፡
  • ማን ይጠራኛል ብለህ ነው?
  • በፊትም እኮ ሳይጠሩ ነበር የሚመጡት፡፡
  • እሱስ ልክ ነህ፣ አሁን ግን የድግስ ሰባሪ መሆን ሰልችቶኛል፡፡
  • በሰላም ነው ግን?
  • ሰላም ነው፣ ሰላም ነው፡፡
  • እኔማ ምን ሆነው እንደጠፉ ስጠይቅ ከቤትም እንደማይወጡ ሰማሁ፡፡
  • እ. . .
  • እንደሰማሁትም ይኸው ቤት ተገኙ፡፡
  • አንዳንዴ ማረፍም አይቻልም እንዴ?
  • የምን እረፍት ነው?
  • በቃ እኔ ማንበብ እወዳለሁ፣ ከዚያም ባለፈ መጻፍ እወዳለሁ፣ ስለዚህ ቤቴ አርፌ እሱን እያደረኩ ነው፡፡
  • ያው ጊዜው የለውጥ ነው ብዬ ነዋ ክቡር ሚኒስትር?
  • ቢሆንስ ማረፍ አይቻልም?
  • በዚህ ጊዜ በከፍተኛ ኃይል መሥራት ነበረብዎት ብዬ ነዋ?
  • እሱንማ እንዳላደርግ የድሮው ሥርዓት ናፋቂ እየተባልኩኝ ሰለቸኝ፡፡
  • እንደዚህማ ተስፋ አይቁረጡ?
  • እኔ ይህቺ አገር 11 በመቶ እንድታድግ ሌት ተቀን ብሠራም፣ የተረፈኝ ስድብና መገለል ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር አገሪቷ እኮ ዕድገት ብቻ ሳይሆን ያስመዘገችው በርካታ ጥፋቶች ተሠርተዋል፡፡
  • የምን ጥፋት ነው?
  • የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ ቢሉ ሙስናውን እያየነው አይደል?
  • ታዲያ እኔ በሙስና የምጠረጠር ሰው ነኝ?
  • እንዴት ማለት?
  • ይኸው የምኖረው እንኳን በመንግሥት ቤት አይደል እንዴ?
  • የራስዎትን ቤትማ አከራይተውት ነዋ?
  • አንድም በስሜ የተመዘገበ ቤት የለኝም፡፡
  • እሱማ ሀብትና ንብረትዎን ጠቅላላ በዘመድ አዝማድ ስም እንዳስመዘገቡት ይታወቃል፡፡
  • ከዚህ ተራ አሉባልታ ለመገላገል ነው እኮ ቤቴ አርፌ የተቀመጥኩት፡፡
  • እንዲህ በቀላሉ ይገላገላሉ ብለው ነው?
  • ደግሞ ሌላ ምን አለ?
  • ያው ሁሉም ሰው ባጠፋው ልክ መሠረት ተጠያቂ ይሆናላ፡፡
  • የሰማኸው ነገር አለ እንዴ?
  • አይ እኔ ስለእርስዎ ሰምቼ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ መንግሥት ፍትሕን አሰፍናለሁ ብሎ አቋም ይዟል ብዬ ነው፡፡
  • እና አንተም አይቀርልህም እያልከኝ ነው?
  • እሱ እንግዲህ ሥራዎት ነው የሚያወጣዎት፡፡
  • በሥራዬማ ንፁህ ነኝ፡፡
  • እሱን ወደፊት እናየዋለን፡፡
  • ልታስፈራራኝ ነው እንዴ የመጣኸው?
  • አመጣጤማ አይጥፉ ለማለት ነው፡፡
  • ነገርኩህ እኮ እኔ ማንበብና መጻፍ ብቻ ነው የምፈልገው፡፡
  • ለመሆኑ ምንድነው የሚያነቡት?
  • ይኸው መደርደሪያውን የሞላው እኮ መጽሐፍ ብቻ ነው፡፡
  • ስለዚህ ይኼ ሁሉ የሚያነቡት መጽሐፍ ነው?
  • እህሳ፡፡
  • እኔም እንግዲህ ያለኝን መጻሐፍ አውስዎታለሁ፡፡
  • ደስ ይለኛል፡፡
  • መደርደሪያዎቹ ላይ ከሚታዩት ግን ለየት ይላል፡፡
  • ምን ዓይነት መጽሐፍ ነው?
  • እኔ መቼም የእምነት ሰው መሆኔን ያውቃሉ?
  • መንፈሳዊ መጽሐፍ ልትሰጠኝ ነው?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን የሚል መጽሐፍ?
  • ሰኔ ጎሎጎታ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከልጃቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • ዳዲ ምክር እንድትመክረኝ ነው የመጣሁት?
  • የምን ምክር ነው?
  • ሰሞኑን በጣም ደስተኛ አይደለሁም፡፡
  • በአገሪቱ ሁኔታ ነው ደስተኛ ያልሆንከው?
  • ኧረ እኔ ምን አገባኝ?
  • ማለቴ በክልሎቹ እሰጣ እገባ ነው ያዘንከው?
  • እኔ የራሴ ክልል ጉዳይ ነው የሚያስጨንቀኝ፡፡
  • ምንድነው ደግሞ የአንተ ክልል?
  • 8B የሚሉት ክፍል ነዋ፡፡
  • 8B ደግሞ ምን ሆነ?
  • ዳዲ ከክፍላችን 8B ወጥተን ትምህርት ቤቱ ውስጥ እንደ ልባችን መጫወት አልቻልንም፡፡
  • ለምን?
  • የትምህርት ቤቱ ሕጎች እየተጣሱ ናቸው፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • ለምሳሌ በእረፍት ሰዓት ተማሪ ወጥቶ መናፈስ አለበት የሚለው ሕግ ተጥሶ እኛ ከክፍል እንዳንወጣ እየተደረገ ነው፡፡
  • ለምንድነው እንዳትወጡ የተባላችሁት?
  • ያው ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ስለሆናችሁ አጥኑ ምናምን ብሎ ነዋ አስተማሪያችን፡፡
  • ታዲያ ለእናተው ጥቅም ነዋ አጥኑ ያላችሁ?
  • ሕጉ በእረፍት ሰዓት ተማሪ ይዝናና እንጂ ያጥና አይልማ?
  • በነገራችን ላይ እኔ ሕግ ይከበር የሚል አቋም ነው ያለኝ፡፡
  • ዳዲ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ የትምህርት ቤቱ ሕግ ይከበር እያለ ነው፡፡
  • ለመሆኑ ትምህርት ቤቱ ውስጥ እንዳትጫወቱ የተደረጋችሁበትን ምክንያት በትክልል ደርሳችሁበታል?
  • እሱማ ርዕሰ መምህራችን ነው እንደዚያ ያስደረገብን፡፡
  • እኮ ለምን አስደረገባችሁ?
  • እኛ ክፍል ውስጥ ያሉ ጥቂት ተማሪዎች በጣም ስለሚበጠብጡ ለትምህርት ቤቱ አሥጊ ናቸው ተብሎ ነው፡፡
  • በጥባጭ ተማሪዎች ክፍላችሁ ውስጥ አሉ?
  • እሱማ በጣም ዱርዬዎችና ለትምህርት ቤቱ አሥጊ የሆኑ ተማሪዎች ክፍላችን ውስጥ አሉ፡፡ ግን ለእነሱ ተብሎ እኛ መቀጣት አለብን?
  • ታዲያ እናንተ ዱርዬ ተማሪዎቹን ለምን አሳልፋችሁ አትሰጧቸውም?
  • እሱንማ ማድረግ አንችልም ዳዲ፡፡
  • ለምን?
  • የክፍላችን ልጆች ላይ እንዴት ነው አቃጣሪ የምንሆነው?
  • ዱርዬዎች እኮ ናቸው?
  • ቢሆንም እሱን ማድረግ ከባድ ነው ዳዲ፡፡
  • ለምን?
  • እንፈራቸዋለን፡፡
  • እ. . .
  • ዳዲ እነዚህ እኮ ከባድ ዱርዬዎች ስለሆኑ በጣም ነው የሚያስፈራሩን፡፡
  • ምን እያሉ ነው የሚያስፈሯሯችሁ?
  • አሳልፋችሁ ከሰጣችሁን ከምድረ ገጽ ትጠፋላችሁ ብለው ነዋ፡፡
  • ታዲያ ምን ልታደርጉ ነው?
  • እኛማ ሕጉ ይከበር ብለን ልንወጣ ነው፡፡
  • ምን ልትወጡ?
  • ሠልፍ ልንወጣ፡፡
  • ሠልፍ ወጥታችሁ ምን ታመጣላችሁ?
  • Selfi እንነሳለን፡፡
  • ለምን?
  • ለፌስቡክ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ቢሮ አንድ ኢንቨስተር መጣ]

  • ክቡር ሚኒስትር ዛሬ ቢሮ የመጣሁት ላመሠግንዎት ነው፡፡
  • ስለምኑ?
  • ክቡር ሚኒስትር ስንት ጊዜ ያስቸገረኝን ነገር ይኸው በእርስዎ ድጋፍ እኮ ተሳካ፡፡
  • እንኳን ደስ አለህ፡፡
  • እንኳን አብሮ ደስ አለን፡፡
  • ሥራውን ከማወቅ የበለጠ ሰው ማወቅ ጥሩ ነው የሚባለው ለዛ ነው፡፡
  • እውነትዎትን ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • በርካታ ሰዎች ያለ እኔ ሥራ ሞክረው ሲወድቁ አይቻለሁ፡፡
  • ግን ክቡር ሚኒስትር እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶች እኮ ለአገር ይጠቅማሉ፡፡
  • ቢሆንም ሰው ማወቅ ወሳኝ ነገር ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከሰው ይልቅ ግን ሲስተም ብንገነባ አይሻልም?
  • ሲስተሙ እኮ ሰዎች ላይ ነው የሚገነባው፡፡
  • እኔ ከእርስዎ ባላውቅም ሲስተም ሲገነባ በሰዎች ላይ ተመርኩዞ ባይሆን ጥሩ ነው፡፡
  • ሲስተም ያለ ሰው ምንም አያደርግም፡፡
  • እኔ ለነገሩ ከእርስዎ አላውቅም፡፡
  • አሁን ምን እያሰብክ ነው?
  • አሁንማ መሬቱም እጄ ገብቷል፣ ፕሮጀክቱም ተፈቅዷል፣ ብድሩም ፀድቋል ወደ ሥራ መግባት ነዋ፡፡
  • ምን ያህል ይፈጅብሃል ወደ ሥራ ለመግባት?
  • ጥቂት ወራት ነው የሚፈጅብኝ፡፡
  • በጣም ጥሩ፡፡
  • ስለዚህ በቀጣይ ጠንክሬ ሠርቼ በኤክስፖርት ዘርፍ አገሬን መጥቀም ነው የምፈልገው፡፡
  • አገሪቱ እኮ እንደ አንተ ዓይነት ባለሀብት ነው የሚያስፈልጋት፡፡
  • እኔ እኮ ለአገሬ ሟች ነኝ፡፡
  • ለውጡ የሚያስፈልገው እንደ አንተ ዓይነቱ ነው፡፡
  • አመሠግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ወደ ውጭ ልትሄድ ነው እንዴ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የያዝከው የምን ሻንጣ ነው ብዬ ነው?
  • ይኼማ ምሥጋናዬን ለመግለጽ ነው፡፡
  • ምንድነው እስኪ ክፈተው?
  • ይኸው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ሆነህ ነው ይኼን ይዘህ የመጣኸው?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አውቀኸዋል ምን እንዳመጣህ?
  • እርስዎን ለማመስገን ያመጣሁት ብር ነው፡፡
  • እኔ እኮ ብር አልቀበልም፡፡
  • በተነገረኝ መሠረት እኮ ነው ብሩን ያመጣሁት፡፡
  • እኔ ብር አልቀበልም አልኩህ እኮ፡፡
  • ይኼንንማ አላምንም፡፡
  • ምኑን ነው የማታምነው?
  • ማለቴ ያለብር የሚሠሩ ሀቀኛ ሚኒስትር ነዎት?
  • እንደ እሱ አልወጣኝም፡፡
  • ታዲያ ምን እያሉ ነው?
  • ብር አልቀበልም፡፡
  • ሌላ የሚቀበሉት ነገር አለ?
  • እኔ የምቀበለው በብር አይደለም፡፡
  • በምንድነው ታዲያ?
  • በዶላር!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ወዳጃቸው ጋር ተገናኙ]

  • ከየት መጣህ ወዳጄ?
  • ልሰናበትዎ ነው የመጣሁት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የምን ስንብት?
  • ጠቅልዬ ከአገር ልወጣ ነው፡፡
  • በሰላም ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር በእርስዎ ላይ ብዙ ተስፋ ጥለን ነበር፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ያው እርስዎ የቀድሞ ሥርዓት ደጋፊ ስለነበሩ ለውጡን ያደናቅፉታል ብለን ተስፋ አድርገን ነበር፤ እርስዎ ግን ከለውጡ ፊት አውራሪዎች ጋር እጅና ጓንት ሆነዋል፡፡
  • ወድጄ እኮ አይደለም፡፡
  • ስለዚህ እርስዎ ለውጡን መቀልበስ ካቃተዎት እኔ እዚህ አገር ምን እሠራለሁ?
  • ከሚመጣው ለውጥ ጋር አንተም ተለውጠህ አትሠራም እንዴ?
  • እሱን ከማድረግ ሞቴን እመርጣለሁ፡፡
  • ምን ሆነህ ነው? ሀብት ቢሉ ሀብት አለህ፣ መሬት ቢሉ መሬት አለህ?
  • አይ መሬት?
  • ምነው እኔ እንኳን ስንት መሬት እንዲሰጥህ አድርጌያለሁ አይደል እንዴ?
  • አሁን ነበረ ነው የሚባለው፡፡
  • እንዴት?
  • ተቀማ ክቡር ሚኒስትር?
  • ያልሠራህበትን መሬት ብትቀማ ምን ችግር አለው?
  • ማን ሠርቶ ያውቅና ነው? ለዚያውም መሀል ቦሌ ላይ የነበረኝ መሬት ቀለጠ፡፡
  • ቢሆንም ሌሎች ቦታዎች አሉ አይደል እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር አንድ አይሉ ሦስት ቦታዎች ነው የተወሰዱብኝ፡፡
  • ምን ተሻለ ታዲያ?
  • አገሪቱ እንደ ዜጋ ስላልቆጠረችኝ እኔም ጠቅልዬ ልሄድ ነው፡፡
  • ውጭ አገር ሄደህ ምን ትሠራለህ?
  • ክቡር ሚኒስትር በደህና ጊዜ ውጭ ያሸሸሁት ገንዘብ ስላለኝ በእሱ እኖራለሁ፡፡
  • ሰሞኑን 36 ቢሊዮን ዶላር ከአገሪቷ ሸሽቷል የሚባለው የአንተም ተጨምሮ ነው?
  • መቼም ዓይኔ እያየ አልበላም?
  • ይኼ አካሄድህ ግን ትክክል አይመስለኝም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር በፊት ከዚህ አገር ምን አተረፍክ ስባል መሬት እል ነበር፡፡
  • አሁንስ?
  • አሁንማ ያተረፍኩት መሬት ሳይሆን ሌላ ነው፡፡
  • ሌላ ምን?
  • ምሬት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ በርካታ ሰዎች ወደ ከተማዋ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ገለጹ

‹‹የኦሮሚያ ክልል መፍትሔ እንዲሰጥበት አሳውቀናል›› የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ‹‹ጉዳዩ...

አይኤምኤፍና ዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የሁለትዮሽ የምንዛሪ ገበያ እንዳይኖር ሊመክሩ ነው

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይኤምኤፍና ዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ያለውን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...