Tuesday, March 28, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ሪሰርቸር ጋር እያወሩ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ባለሀብት ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ምንድነው የሚሠራው?
  • ምንድነው የሚሠራው ማለት?
  • እኛ እኮ ሌላ አገር የለንም፡፡
  • አንተ አሁንም ትቀልዳለህ አይደል?
  • የምን ቀልድ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ሦስት ፓስፖርት አይደለም እንዴ ያለህ?
  • ክቡር ሚኒስትር እትብቴ የተቀበረው ግን እዚሁ ነው፡፡
  • ለምን ታዲያ የሌላ አገር ዜግነት ኖረህ?
  • እኔ ፓስፖርቴን ለመቅደድም ዝግጁ ነኝ፡፡
  • እሱን እንኳን ተወው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ሌሎቹ እኮ የወረቀት አገሮቼ ናቸው፣ ኢትዮጵያ ግን የልቤ አገር ናት፡፡
  • ታዲያ ኢትዮጵያ ምን ሆነች?
  • ከዚህች አገር የት እንድንሄድ ነው የምትገፋፉን?
  • ማን ገፋህ?
  • ትልቅ ቦታ ለመድረስ አይደል እንዴ የሁላችንም ጥረት ክቡር ሚኒስትር?
  • እውነት ነው፡፡
  • ታዲያ የት ሄደን ምን እንሥራ?
  • አልገባኝም፡፡
  • በጣም ነው ያዘንኩት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑ ነው ያሳዘነህ?
  • ወሰዱት እኮ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምኑን?
  • መሬቱን ነዋ፡፡
  • አንተ በየቦታው አይደል እንዴ መሬት ያለህ?
  • ይኸው ሁሉንም እኮ ነው ጠራርገው የወሰዱት፡፡
  • ታዲያ መገንባት ነበረብሃ?
  • እኔ እኮ በርካታ ዜጎችን ቀጥሬ የማሠራ ባለሀብት ነኝ፡፡
  • ለዚያ እኮ ነበር መሬቱ የተሰጠህ፡፡
  • ታዲያ መሥሪያ ጊዜ ሊሰጠኝ ይገባ ነበር፡፡
  • አንተ ግን አጥረህ ብድር ስትጠይቅበት ነበር፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የተወሰደብኝ መሬት እኮ አንድ ክፍለ ከተማ ያክላል፡፡
  • አሁን ምን ይደረግ ነው የምትለው?
  • ክቡር ሚኒስትር መሬቴ እንኳን ይወሰድ፣ በሁሉም ላይ እንደወሰናችሁት ገብቶኛል፡፡ እኔ ግን ምን በልቼ እንዳድር አስባችሁ ነው?
  • ማለት?
  • ቢዝነሴም ታግዷል፡፡
  • ታግዷል ስትል?
  • ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳላደርግ ቢዝነሴ ታግዷል፡፡
  • ለምን?
  • እኔ ምን አውቃለሁ ክቡር ሚኒስትር? ምን ባጠፋ ነው እንደዚህ የምታደርጉት?
  • እንግዲህ ቢዝነስህ የታገደበት በቂ ምክንያት ይኖራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
  • እኮ ምን አጠፋሁ?
  • አሁንም አንተ ከቀድሞው ሥርዓት ጋር ያለህ ቁርኝት እንደጠነከረ ነው አይደል?
  • እሱማ ይኼ ሁሉ ሀብት የመጣው በዚያ ነው፡፡
  • ይኼን ሁሉ ሠርተህ እንዳማታመጣውማ ግልጽ ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከቀድሞው ሥርዓት ጋር እኮ በጋብቻ ሳይቀር የተዛመድኩ ነኝ፡፡
  • ከጋብቻው በላይ እኮ የሙስናው ዝምድና ይበልጣል፡፡
  • እሱስ ልክ ነዎት፡፡
  • ስለዚህ አሁንም ከድሮው ሥርዓት ጋር ያለህ ግንኙነት አልተቋረጠም፡፡
  • ምን ባደርግ ይሻላል?
  • ቶሎ ከአገር ውጣ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ከኤርፖርት እኮ ነው የመለሱኝ፡፡
  • አንተ ሦስት ፓስፖርት አይደል እንዴ ያለህ?
  • በየትኛውም ፓስፖርቴ መውጣት አልቻልኩም፡፡
  • እኔ ምን ላድርግህ  ታዲያ?
  • የት ልትግባ ክቡር ሚኒስትር? ምከሩኝ እስኪ?
  • ለምን ገዳም አትገባም?
  • እዚያም አውቀውኝ አባረሩኝ፡፡
  • እንግዲያው መግባት ያለብህ አንድ ቦታ ነው፡፡
  • የት ክቡር ሚኒስትር?
  • ገደል!

[ክቡር ሚኒስትር ቢሮ አማካሪያቸው ገባ]

  • ምነው ክቡር ሚኒስትር ፊትዎ ጠቆረብኝ?
  • ኧረ ተወኝ፡፡
  • ምን ተፈጠረ?
  • እስኪ ተወው፡፡
  • ምን ሆኑ?
  • አንድ የሚያስደነግጥ ዜና ሰምቼ ነው፡፡
  • የምን ዜና?
  • አባረሩት እኮ፡፡
  • ማንን?
  • ዋናውን ቆራጡ መሪያችንን ነዋ፡፡
  • ለምንድነው የሚያስደነግጡኝ ክቡር ሚኒስትር ማን ነው የተባረረው?
  • አንተ ለመሆኑ ሚዲያ ትከታተላለህ?
  • ኧረ በጣም ነው የምከታተለው፡፡
  • ታዲያ እንዴት መባረሩን አልሰማህም?
  • እኔ እንግዲህ ዛሬም ሶሻል ሚዲያ ስከታተል ነበር የተባረረ ወሬ አልሰማሁም፡፡
  • ሁሌም ተዓማኒ የዜና ምንጮችን ተከታተል የምልህ ለዚህ ነው፡፡
  • ለመሆኑ ማን ነው የተባረረው?
  • ጆዜ ሞሪኖ ነዋ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የእሱ መባረር ይኼን ያህል አንገብጋቢ ነው እንዴ?
  • ጉዳዩ የገባህ አይመስለኝም፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰውዬው እኮ ክለቡን ወደ ተሻለ ዕድገት የሚያሸጋግረው መሪ እንደነበር ማንም ያውቀዋል፡፡
  • እኔ እንደሰማሁት ግን ቡድኑን ችግር ውስጥ የከተተው እሱ ነው የሚል ነው፡፡
  • እንዳትሳሳት፣ ሞሪኖ የባለ ዕራዩን መሪ አሌክስ ፈርጉሰንን ሌጋሲ ለማስቀጠል ወሳኝ ሥራ ሊሠራ የነበረ አሠልጣኝ ነው፡፡
  • እ. . .
  • በክለቡ ውስጥ ትክክለኛ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን ፍልስፍና ሰርፆ እንዲቀጥል አድርጓል፡፡
  • እንዴት?
  • ተጨዋቾቹ ከአሠልጣኙ ብቻ የሚሰጣቸውን ትዕዛዝ እንዲፈጽሙ በማድረግ የፈርጉሰንን አመራር አስቀጥሏል፡፡
  • ስለዚህ ሊባረር አይገባም ነበር እያሉ ነው?
  • የራስህ እግር ላይ እንደ መተኮስ ነው ስልህ?
  • ክቡር ሚኒስትር እርስዎ ግን ከዘመኑ ጋር መራመድ የቻሉ አልመሰለኝም፡፡
  • እንዴት?
  • በቃ የእርስዎ እኩዮችና እርስዎ እንደ ድሮው በአፈና በጭቆና ምናምን ነው መግዛት የምትወዱት፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • አሁን የእግር ኳስ ፍልስፍና ተቀይሯል፡፡
  • ወደ ምን?
  • ወደ ፍቅር፣ መደመር፣ አንድነት ነዋ፡፡
  • የማታውቀውን ነገር አትዘባርቅ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር የሊቨርፑልና የማንቸስተር ሲቲ አሠልጣኞች በዚህ ፍልስፍና ነው ውጤታማ የሆኑት፡፡
  • ለእኔ ከሞሪኖ የሚበልጥ አሠልጣኝ የለም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ሰውዬው እኮ የክለቡን ሀብት አባክኗል፡፡
  • እንዴት አድርጎ?
  • ይኸው ለስምንት ተጨዋቾች ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ አውጥቶ ግዥ ፈጽሟል፡፡
  • ለክለቡ ሲል ነዋ፡፡
  • ስነግርዎት ያለዕቅድና ፍላጎት ነው የሚገዛው፡፡
  • ይኼን እንኳን አልቀበልም፡፡
  • እንዲያውም በዚህ ምክንያት ቅፅል ስም ወጥቶለታል፡፡
  • ማን ተባለ?
  • ሜቴክ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ሪሰርቸር ጋር እያወሩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ለውጡን እንዴት እያዩት ነው?
  • ለውጡ ጥሩ ነው ግን የሚጎድሉት በርካታ ነገሮች አሉት፡፡
  • ምንድነው የሚጎድለው?
  • ትግሉ አሁንም አልቆመም፡፡
  • የምን ትግል?
  • በረሃም ታግለናል፣ አሁንም እንታገላለን፡፡
  • ለምንድነው የምትታገሉት?
  • የዕለት ተዕለት ኑሮን ከማሸነፍ ጀምሮ በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ነዋ፡፡
  • አሁንም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አልተገነባም ብለው ነው የሚያስቡት?
  • አንተ ተገንብቷል ልትለኝ ነው?
  • እየተገነባ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት ሆኖ?
  • በፊት እኮ ለየት ያለ የፖለቲካ አመለካከት የነበረው ዜጋ ምን እንደሚደረግ እናውቃለን?
  • እ. . .
  • የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት እስር ቤት ነበር የሚኖሩት፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • መንግሥትን የሚቃወሙ ጋዜጠኞች ወይም ብሎገሮች ማዕከላዊ ነበር ቤታቸው፡፡
  • ያኔ የነበረው አሠራር የዓለምን ፖለቲካ የሚያንፀባርቅ ነበር፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ዓለም በአሸባሪዎች ላይ ጦርነት ስላወጀ እኛም የሚያሸብሩንን እስር ቤት እንከት ነበር፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እሱን እንኳን ተውት፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ይኸው አሁን ከበፊቱ በባሰ ሁኔታ መንግሥት ቢሰድብም፣ የትኛውም ግለሰብ በሐሳቡ ምክንያት እየታሰረ አይደለም፡፡
  • ምነው ጓደኞቻችን አንድ ክልል ውስጥ ታስረው አይደል እንዴ ያሉት?
  • እነሱን ያሰራቸው የራሳቸው ሐሳብ ነው፡፡
  • ስማ በአሁኑ ወቅት ሕገ መንግሥቱ እየተጣሰ መሆኑን አታውቅም?
  • መጀመርያ ሕገ መንግሥቱን ማን ነበረ የሚጥሰው?
  • እኛው፡፡
  • ታዲያ አሁን መጣሱ ምን ይገርማል?
  • ለሕዝቡ በአንዴ ዴሞክራሲን በአካፋ እየዛቅህ አትሰጥም፡፡
  • አልገባኝም?
  • ዴሞክራሲን በማንኪያ ለለመደ ሕዝብ በአንዴ በቡልዶዘር ዝቀህ ስትሰጠው ይኸው አገሪቱ ተተራመሰች፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ሕዝቡ ዴሞክራሲ በዛብኝ ብሎ አያውቅም፡፡
  • ዴሞክራሲ መቼ አግኝቶ ያውቅና?
  • አሁንማ ሕዝቡ የመናገር መብቱን ተጠቅሞ ዴሞክራሲያዊ መብቱን እያጣጣመ ነው፡፡
  • አገሪቱ ውስጥ ዴሞክራሲ አለ እያልክ ነው?
  • በሚገባ፡፡
  • አንተ ስለዴሞክራሲ ያለህ አመለካከት የተሳሳተ ነው፣ ለዚያ ነው እኛም እየታገልን ነው ያልኩህ፡፡
  • ቆይ ለእርስዎ ዴሞክራሲ ማለት ምን ማለት ነው?
  • አንድና አንድ ነገር ሲሆን ነው፡፡
  • ምን ሲሆን?
  • የድሮው ሥርዓት ሥልጣን ላይ ሲወጣ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ወዳጃቸው ደወለላቸው]

  • በቲቪ ዓይቼዎት ነው እኮ የደወልኩልዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የትኛው ቻናል ላይ?
  • ምን ቻናል ላይ ብቻ አሁንማ በየሶሻል ሚዲያውም የእርስዎን ቪዲዮ ሕዝቡ እየተቀባበለው ነው፡፡
  • ምንድነው ያየኸው?
  • ፕሮቶኮል የሚባል ነገር አያውቁም እንዴ?
  • እኔ በፊትም ስለአለባበሴ ግድ እንደሌለኝ ታውቃለህ?
  • እኔ ስላለባበስዎ አይደለም፡፡
  • ታዲያ የምን ፕሮቶኮል ነው?
  • በአጠቃላይ ሥነ ሥርዓትዎና ሕዝብ ፊት ስለሚያደርጉት ድርጊት ሊጠነቀቁ ይገባል፡፡
  • ሳንቀላፋ ታየ እንዴ በቲቪ?
  • አላንቀላፉም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ጥፍሬን መብላት ደግሞ ሚስቴ አስትታኛለች፡፡
  • እርስዎ ጥፍር ይነቅላሉ እንጂ መቼ ጥፍር ይበላሉ?
  • ታዲያ ስልኬን ስነካካ ዓይተኸኝ ነው?
  • እኔ እሱን አይደለም የምልዎት፡፡
  • ታዲያ ምንድነው?
  • ቲቪ ላይ በተደጋጋሚ ስለሚቀርቡ ፕሮቶኮልዎን መጠበቅ አለብዎ፡፡
  • እኮ የምን ፕሮቶኮል?
  • ለማንኛውም እኔ በራሴ ወጪ ላስተምርዎ ወስኛለሁ፡፡
  • ምንድነው የምታስተምረኝ?
  • ማጨብጨብ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ...

‹‹ኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ውጫዊ ጫናዎችን ለመቀልበስ የፖሊሲ ሪፎርሞች ያስፈልጋሉ›› ዓለም ባንክ

በዓለም ደረጃ ከተፈጠረው የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ጋር በተገናኘ፣ በኢትዮጵያ ውጫዊ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...