Saturday, June 10, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየስፖርት ማዕከላትና አካዴሚዎች ከፌዴሬሽኖች ጋር ያላቸው ክፍተት እየጎላ መምጣቱ ተገለጸ

የስፖርት ማዕከላትና አካዴሚዎች ከፌዴሬሽኖች ጋር ያላቸው ክፍተት እየጎላ መምጣቱ ተገለጸ

ቀን:

በኢትዮጵያ የሚገኙ የማሠልጠኛ ማዕከላትና አካዴሚዎች ከፌዴሬሽኖችና ከክለቦች ያላቸው ግንኙነት ክፍተት እንዳለው ተገለጸ፡፡

በስፖርት ኮሚሽን በስፖርት ትምህርቶችና ሥልጠና የዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በአዳማ ከተማ ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም. በተሰናዳው መድረክ ላይ የስፖርት አካዴሚዎቹ ሥልጠና መስጠት ቢችሉም ከፌዴሬሽኖች ጋር ክፍተት በመኖሩ ስፖርተኞችን በአግባቡ ማብቃት እንዳልተቻለ ተገልጿል፡፡

በአትሌቲክስ በመካከለኛ ርቀት፣ በረዥም ርቀት እንዲሁም በሜዳ ተግባር ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ ሥልጠናቸው እያከናወኑ ያሉት አካዴሚዎቹ ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ስላፈሯቸው ታዳጊዎችና ውጤቶች እንዲሁም ችግሮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በአዲስ አበባ የሚገኘውን የወጣቶች ስፖርት አካዴሚ፣ በአሰላ የሚገኘው የጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዴሚ፣ እንዲሁም በቆጂ፣ ማይጨው፣ ሀገረ ሰላም፣ ደብረ ብርሃንና የአምቦ ጎል ማሰልጠኛ ማዕከሎች የሦስት ዓመት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል:: በሪፖርታቸውም በሦስት ዓመታት ውስጥ በአገሪቷ ለሚገኙት ክለቦች፣ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ለብሔራዊ ቡድን በርካታ አትሌቶችን ማበርካታቸውን በየደረጃው አብራርተዋል:: ከሥልጠናው ባሻገርም በዘርፉ በቂ የሥልጠና ቁሳቁሶች፣ ባለሙያዎች፣ የውድድር ሥፍራዎች፣ አትሌቶች ከክለቦች ጋር የሚያደርጉት ሕገወጥ ግንኙነትና የቀን የምግብ ወጪ እንዲሁም የኪስ ገንዘብ በቂ ያለመሆንና በቂ የማዘውተሪያ ቦታ አለመኖር በሥልጠና ተቋማቱ ከፍተኛ እንቅፋቶች መሆናቸው ተጠቅሰዋል::

በአገሪቱ የሚገኙ የስፖርት የሥልጠና ማዕከላትና አካዴሚዎች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ ማድረግ እንደሚገባቸው የስፖርት ምክትል ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው ባልቻ አሳስበዋል:: የልምድ ልውውጡ በዋናነት መሠረት የሚያደርገው በማዕከላትና በአካዴሚዎች የሚሰጡ ሥልጠናዎች ቅንጅታዊ አሠራርና ውጤታማነትን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡

በተለይ አትሌቲክሱ ዘርፍ ከፍተኛ ወጤት ማምጣት መቻሉ አህጉርና አገር አቀፍ ወጤቶች ተጠቅሰዋል:: በተለይ በእግር ኳስና በአትሌቲክስ ሥልጠና ሒደት ከፍተኛ ውይይት እየተደረገ ሲሆን፣ በመድረኩ የኢትዮጵያ አትሌቲክስና የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ቢጋበዙም አለመገኘታቸውን ስፖርት ኮሚሽኑ አስታውቋል:: የሥልጠና ማዕከላትና የአፈፃፀም ሪፖርቱን ተከትሎም አዲስ ማሻሻያዎች እንደሚኖሩ ይጠበቃል::

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አያሌ የውኃ “ጠርሙሶች”ን በጫንቃ

መሰንበቻውን በአይቮሪ ኮስት መዲና አቢጃን የምትኖር አንዲት ሴት፣ በሚደንቅ...

ወልቃይትን ማዕከል ያደረገው የምዕራባዊያን ጫና

በትግራይ ክልል የተከሰተው የዕርዳታ እህል ዘረፋ የዓለም አቀፍ ተቋማት...

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...