Sunday, March 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

የክቡር ሚኒስትሩ ልጆች ግቢው ውስጥ ሲጨቃጨቁ ክብር ሚኒስትሩ ወጡ

[የክቡር ሚኒስትሩ ልጆች ግቢው ውስጥ ሲጨቃጨቁ ክብር ሚኒስትሩ ወጡ]

  • ምን ሆናችኋል ልጆች?
  • ምነው ዳዲ?
  • በጣም እየረበሻችሁኝ ነው ማረፍ አልችልም እንዴ?
  • ይቅርታ ዳዲ፡፡
  • ምንድነው የሚያጨቃጭቃችሁ?
  • የማን ይቁም የሚለው ላይ መስማማት አቅቶን ነው፡፡
  • ምንድነው የሚቆመው?
  • ሐውልት፡፡
  • የምን ሐውልት?
  • በቃ ለቤተሰባችን መታሰቢያ የሚሆን ሐውልት ማቆም ፈልገን ነው፡፡
  • የት?
  • እዚህ ግቢ ውስጥ፡፡
  • ለምንድነው ሐውልት ማቆም የፈለጋችሁት?
  • ያው ቤተሰባችን በጣም ስኬታማ ስለሆነ ለማስታወሻ ግቢ ውስጥ ሐውልት ቢቆም ብለን ነው፡፡
  • ይኼ እኮ የመንግሥት ቤት ነው፡፡
  • የመንግሥት ቢሆንም ይህ ቤተሰብ በአገር ደረጃ ራሱ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ስለሆነ ሐውልቱ ቢቆም ችግር የለውም፡፡
  • ለመሆኑ አንተ የማን ሐውልት ይቁም ነው ያልከው?
  • እኔማ የአያታችን ሐውልት መቆም አለበት እያልኩ ነው፡፡
  • ለምን እሱን መረጥከው?
  • ዳዲ የዚህን ቤተሰብ ህዳሴ ያመጣው ማን ነው?
  • እሱስ ልክ ነህ፡፡
  • በዚያ ላይ የቤተሰቡ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግ ያደረገው ማን ነው?
  • እሱ ነበር፡፡
  • ለቤተሰባችን ጤናማ የሕይወት ዘይቤን ያስተማረን እሱ እኮ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • ሁሉም የቤተሰቡ አካል በየግቢው አረንጓዴ ቦታ እንዲኖረው ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡
  • እሱስ እውነትህን ነው፡፡
  • በዚያ ላይ ሁላችንም አመጋገባችን ሳይቀር አረንጓዴ እንዲሆን አድርጓል፡፡
  • ልክ ብለሃል፡፡
  • ስለዚህ የቤተሰባችን ወኪል ሆኖ ሐውልት ሊቆምለት የሚገባው እሱ ነው፡፡
  • አንቺስ ምንድነው ሐሳብሽ?
  • የአያታችን ሐውልት ሊቆም አይገባም ባይ ነኝ፡፡
  • ለምን?
  • በእርግጥ እኔ አያቴን እወደዋለሁ፣ ግን እሱ ከወንድሙ ጋር በመጣላቱ ምክንያት ነው እስካሁን ቤተሰቡ የተከፋፈለው፡፡
  • . . .
  • እንዲያውም አንተ ነህ እኮ አስታርቀሃቸው ሰላም መውረድ የቻለው፡፡
  • እሱስ ልክ ነሽ፡፡
  • ስለዚህ የእሱ ሐውልት እዚህ ሊቆም አይገባም፡፡
  • የማን ሐውልት ይቁም እያልሽ ነው ታዲያ?
  • የቅድመ አያታችን ነዋ ዳዲ፡፡
  • አንቺ የት ታውቂዋለሽ እሱን?
  • እንዴ ዳዲ ይኼ ቤተሰብ እንዲሰባሰብ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ የነበረው እሱ አይደል?
  • በምን አወቅሽ?
  • ዳዲ ትልቁን የቤተሰባችንን ማኅበር የመሠረተው እሱ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡
  • ይኼን ማን ነገረሽ?
  • ሁሌ ማኅበራችን ላይ ሲወራ እሰማለሁ፡፡
  • እሱስ ልክ ነሽ፡፡
  • እንዲያውም አያታችን በቅድመ አያታችን ይቀና እንደነበር አውቃለሁ፡፡
  • ወይ የዛሬ ልጆች?
  • እውነቴን አይደል ዳዲ?
  • አሁን ምን እያላችሁ ነው?
  • እኔ የአያታችን ሐውልት ይቁም እያልኩ ነው፡፡
  • አንቺስ?
  • እኔማ የቅድመ አያታችን ሐውልት ነው መቆም ያለበት የምለው፡፡
  • ለማንኛውም እዚህ መቆም ያለበት ሐውልት የማን እንደሆነ ታውቃላችሁ?
  • የማን ነው?
  • የእኔ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ደላላ ወዳጃቸው ጋ ደወሉ]

  • አንተ ሰውዬ ምን ሆነሃል?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ስልክ ብደውል ብደውል አታነሳም እኮ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ቢዚ ሆኜ ነዋ፡፡
  • ምንድነው ቢዚ ያደረገህ?
  • ስብሰባው ነዋ፡፡
  • የምን ስብሰባ?
  • የመሪዎቹ ስብሰባ ነዋ፡፡
  • ጉረኛ አንተ ደግሞ ምን አገባህ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር ዋናው የዶላር ሥራ አሁን አይደል እንዴ?
  • እሱን ስታጧጡፍ ነዋ ሌላኛውን ቢዝነስ የዘነጋኸው?
  • የቱን ቢዝነስ ክቡር ሚኒስትር?
  • ስብሰባው ላይ እኮ አንድም የእኛን መኪና አላየሁም፡፡
  • የእኛ መኪኖችማ ሁሌም ሥራ ላይ ናቸው፡፡
  • አንድም አላየሁም ስልህ?
  • ማለቴ ከተማ ውስጥ እኮ የታክሲ አገልግሎት ይሰጣሉ፡፡
  • ምን ነካህ እነዚያን ዘመናዊ መኪኖች ታክሲ እያሠራሃቸው ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር የከተማችን የታክሲ አገልግሎት እኮ ዘመናዊ ሆኗል፡፡
  • እሺ እነዚያ ዘመናዊ ቫኖች ምን እየሠሩ ነው?
  • እነሱም ስኩል ባስ ሆነዋል፡፡
  • ተማሪ ማመላለሻ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዴት እነዚያን መኪኖች የተማሪዎች ማመላለሻ ታደርጋቸዋለህ?
  • ክቡር ሚኒስትር ተማሪዎች እኮ የወደፊቱ ተስፋ ናቸው፡፡
  • ዲስኩርህን እዚያው፡፡
  • ምን አጠፋሁ ክቡር ሚኒስትር?
  • መኪኖቹን ለተሰብሳቢዎቹ ባለማከራየትህ እኮ ዶላር ነው ያስመለጥከኝ?
  • ክቡር ሚኒስትር አልተደመሩም እንዴ?
  • የምን መደመር ነው?
  • አሁን ቅድሚያ የሚሰጠው እኮ ለዜጋ ነው፡፡
  • በዶላር ቀልድ የለም ስልህ?
  • ካሉ እሺ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለማንኛውም በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ገብቶኛል፡፡
  • ምን ሊያደርጉ?
  • ማለቴ የስብሰባ ተሳታፊዎቹ መኪና እንዳይከራዩ ማድረግ አለብኝ፡፡
  • ታዲያ ከተማ ውስጥ በምን ይንቀሳቀሱ?
  • በታክሲ!

[ክቡር ሚኒስትሩ በቅርቡ የታሰሩ ጓደኛቸውን ሊጠይቁ እስር ቤት ሄዱ]

  • እንዴት ነህ ወዳጄ?
  • ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሰላም ነህ?
  • ምን ሰላም አለ ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን ሆንክ?
  • መድኃኒት የለ፣ መጽሐፍ የለ፣ ሰው እንደ ልቡ መጥቶ አይጠይቀኝ፡፡
  • ይኸው እየመጣሁ እጠይቅሃለሁ አይደል እንዴ?
  • በፊት እየመጣ የሚሰግድልኝ ሁሉ አሁን የታለ?
  • የሚሰግደው ተገዶ እንጂ ወዶ መሰለህ?
  • በቃ በጣም መሮኛል፡፡
  • ምን ሆነህ?
  • እኔ እኮ ትልቅ ነገር ፈልጌ አይደለም፡፡
  • እኮ ምንድነው የፈለግከው?
  • ያው እስር ቤት ያለው ምግብ አልተመቸኝም፡፡
  • ምን ሆነብህ?
  • ደም ግፊቱ፣ ስኳሩም ስላለብኝ ጨው የሌለበት ምግብ መመገብ አልችልም፡፡
  • ታዲያ እንዲስተካከልልህ አትነግራቸውም?
  • ማን ይሰማኛል ብለው ነው? በዚያ ላይ እኔ የለመድኩት ዓይነት ምግብ ነው፡፡
  • ታዲያ እዚህ ሼፍ እንዲቀጠርልህ ፈልገህ ነው?
  • ለአገር ካበረከትኩት አንፃር እሱ ሲያንሰኝ ነው፡፡
  • ቀልደኛ ነህ እባክህ?
  • በዚያ ላይ መጽሐፍ ማንበብ እንደምወድ ያውቃሉ አይደል?
  • ታዲያ መጽሐፍ እየገባልህ አይደል እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር ከዘመኑ ጋር መራመድ አለብን፡፡
  • እንዴት?
  • አሁን እኮ ብዙ ነገር የሚነበበው ኢንተርኔት ላይ ነው፡፡
  • . . .
  • ኦንላይን እኮ ነው ማንበብ የምፈልገው፡፡
  • ኦንላይን?
  • አዎን ምነው?
  • እውነትም ብሶብሃል፡፡
  • ምኑ?
  • ዕብደቱ፡፡
  • በዚያ ላይ እኔ ስፖርት መሥራት የለመድኩት ጂም ነው፡፡
  • እሺ ሌላስ?
  • በየሳምንቱ ስቲምና ሳውና መጠቀምም እወዳለሁ፡፡
  • በጣም ተቸግረሃልና?
  • ታዲያስ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ይሻላል ታዲያ?
  • እኔማ ከሌሎችም አገሮች ቢሆን ልምድ ብትወስዱ ባይ ነኝ፡፡
  • የምን ልምድ?
  • ማለቴ እስር ቤቴን ብትቀይሩልኝ፡፡
  • የት መታሰር አማረህ?
  • ሆቴል!

[ለክቡር ሚኒስትሩ ከሥልጣን የወረዱ ሚኒስትር ደወሉላቸው]

  • ሄሎ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሄሎ ማን ልበል?
  • ማን ልበል?
  • አዎን ማን ልበል?
  • እርስዎም ማን ልበል ማለት ጀመሩ?
  • ይቅርታ ከየት ነው የተደወለው?
  • ያኔ በቀን አሥሬ እንዳልደወሉልኝ አሁን ማን ልበል ይሉኛል ክቡር ሚኒስትር?
  • እስካሁን አላወቅኩህም፡፡
  • ለማንኛውም የቀድሞ ወዳጅዎ ነኝ፡፡
  • ውይ ቁጥርህ እኮ ተቀይሮብኝ ነው፡፡
  • እርስዎም ረሱኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ኧረ ሁሌ ልደውል አስባለሁ፡፡
  • ቢያስቡኝማ ይደውሉ ነበር ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሁሌ ነው የማስብህ ስልህ?
  • ይኸው ድምፄን ራሱ መቼ ለዩት?
  • ከሥልጣን ስትወርድ የአንተም ድምፅ ተቀይሯል መሰለኝ፡፡
  • እንደዚህ የእርስዎም መቀለጃ ሆንኩ፡፡
  • ኧረ እየቀለድኩብህ አይደለም፡፡
  • ትዝብት ነው ትርፉ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ኧረ ሁሌ ከሚስቴ ጋር ስለእናንተ ነው የምናስበው፡፡
  • ቢያስቡማ ኖሮ ይደውሉልኝ ነበር፡፡
  • ያው እናንተ ጋ መደወል ችግር ነው ብዬ ነው፡፡
  • ይኸው እኔ እየደወልኩ አይደል እንዴ?
  • የሚገርምህ አሁን አንተ መሆንህን ሳውቅ መፍራት ጀመርኩ፡፡
  • ለማንኛውም በፊት እንደዚያ ጠብ እርግፍ እንዳላሉልኝ በአንዴ ይዝጉኝ?
  • ለመሆኑ ሌሎቹስ እንዴት ናቸው?
  • ኧረ ሌሎቹም ተቀይሞዎታል፡፡
  • ምን አጠፋሁ?
  • መቼ ዞር ብለው ዓይተውን ያውቃሉ?
  • ይቅርታ በሉልኝ፡፡
  • ይቅርታ ኪስ አይገባም ሲባል አልሰሙም፡፡
  • ምን ልቀጣ ታዲያ?
  • እዚህ ያረፍነው ሆቴል መሆኑን ያውቃሉ አይደል?
  • አዎን ሰምቻለሁ፡፡
  • የሆቴል ወጪያችን ከፍተኛ እየሆነ ነው፡፡
  • ምን ይደረጋል ታዲያ?
  • ስለዚህ ሰሞኑን እንልክልዎታለን፡፡
  • ምኑን?
  • ቢሉን!

 

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው ከፍተኛ ሀብት ጥቅም ላይ እየዋለ አይደለም ተባለ

በኢትዮጵያ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የተሰበሰበው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን...

ጥቁር የመልበስ ውዝግብና የእምነት ነፃነት በኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ኅዳር ወር ላይ በፓርላማ...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...

ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ የአዲስ አበባን ንግድና ዘርፍ ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት በተደረገው ምርጫ አሸነፉ

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤትን በፕሬዚደንትነት ለመምራት፣...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...