Monday, March 20, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ለደላላ ወዳጃቸው ስልክ ደወሉ

[ክቡር ሚኒስትሩ ቢሮ ሲገቡ ከጸሐፊያቸው ጋር ተገናኙ]     

  • አንቺ ምን አደረኩሽ?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ያስቀየምኩሽ ነገር አለ እንዴ?
  • ኧረ በፍጹም፡፡
  • እውነቱን ንገሪኝ?
  • ኧረ የለም፣ ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ታዲያ ለምን አልነገርሽኝም?
  • ምኑን ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰው ሁሉ አይደል እንዴ የሰማው?
  • እኮ ምኑን?
  • ኮንዶሚኒየም ቤት እንደደረሰሽ ነዋ፡፡
  • እ… እሱን ነው፡፡
  • ታዲያ ምን አድርጌሽ ነው?
  • ኧረ ምንም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼን የመሰለ ደስታ ለምን አላካፈልሽኝም ታዲያ?
  • ደስታ ነው ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ከቤት በላይ ምን ደስታ አለ ብለሽ ነው?
  • እሱስ ልክ ነበሩ፡፡
  • ታዲያ ምንድነው የምትይው?
  • ደስታችን ላይ ውኃ ቸለሱበት እንጂ፡፡
  • ማን ነው ውኃ የቸለሰበት?
  • የክልሉን መንግሥት መግለጫ አላዩትም እንዴ?
  • እሱንማ አይቼዋለሁ፡፡
  • ታዲያ ደስታችን ላይ ውኃ ከዚህ በላይ እንዴት ይቸልሱበት?
  • ቆይ ተረጋጊ፡፡
  • አሁንማ ተፋስ ቆረጥኩ፡፡
  • ለምን ትቆርጫለሽ?
  • ክቡር ሚኒስትር መግለጫው እኮ ስለኮዬ ፈጬ ብቻ አይደለም፡፡
  • ሌላ ምን አለበት ደግሞ?
  • ስለ ኮልፌና ቀጨኔ ነዋ፡፡
  • መቼም አንቺ ነገረኛ ነሽ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር መግለጫው እኮ አዲስ አበባም የእኛ ናት ይላል፡፡
  • እሱማ ሰሞነኛ ፖለቲካ ነው፡፡
  • ለእኛ ግን ፖለቲካ ሳይሆን ሥጋት ነው፡፡
  • ብዙ አትሥጊ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቼዋለሁ፡፡
  • ምን እያልሽ ነው?
  • ይኸው እኔማ ቤት ደረሰኝ ብዬ ዕቁብም ተቀብዬ ነበር፡፡
  • ሁለተኛ የደስ ደስ ገጥሞሻላ፡፡
  • ምን ያደርጋል ክቡር ሚኒስትር?
  • ምነው?
  • ዕቁቡን የተቀበልኩት እኮ የቤት ዕቃ ለመግዛት ነበር፡፡
  • ገዛሽበት ታዲያ?
  • እንዴት አድርጌ?
  • ምነው?
  • እኔማ ቤቱን እረከባለሁ ብዬ ነበር ዕቃ ለመግዛት ያሰብኩት፡፡
  • አሁን ተውሽው ታዲያ?
  • መግለጫው እኮ ከባድ ነው፡፡
  • ፖለቲካ ነው ስልሽ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ፖለቲካ ብቻ አይመስለኝም፡፡
  • እንዴት?
  • ቤቱን ላይ ስሄድ የሰማሁት ተስፋ አስቆረጠኝ፡፡
  • ምን ሰማሽ?
  • መቼ ዕለት ሄጄ ስጎበኝ የአካባቢው ወጣቶች ምን እንዳሉኝ ያውቃሉ?
  • ምን አሉሽ?
  • ቤቱ የማን እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡
  • የእኔ ነው አልሻቸው?
  • እንደዚያ ስላቸው ምን ቢሉኝ ጥሩ ነው?
  • ምን አሉሽ?
  • የእኛ ነው!

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ ባለሀብት ጋ ይደውላሉ]

  • ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት ነህ ወዳጄ?
  • ዛሬ ከየት ተገኙ?
  • እኔ እኮ ሁሌም ላገኝህ እየፈለኩ ሥራ ስለሚበዛብኝ ነው፡፡
  • ምነው በሰላም?
  • እንደው ስለአጠቃላይ ሁኔታው እንድንነጋገር ብዬ ነው፡፡
  • ስለምኑ ክቡር ሚኒስትር?
  • ስለአገራችን ነዋ፡፡
  • አገራችንማ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ናት፡፡
  • ምን ሆነች?
  • መቼም ከአገር አልወጡም አይደል?
  • የት እወጣለሁ ብለህ ነው?
  • ታዲያ እዚሁ ከሆኑማ የችግር መፈልፈያ ሆናለች አይደል እንዴ?
  • ተው አታሟርትባት፡፡
  • እያሟረትኩባት አይደለም፡፡
  • ምን እያደረክ ነው ታዲያ?
  • ሀቁን ነው የነገርኩዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አንተ እኮ ቢያንስ ባለሀብት ነህ፡፡
  • ብሆንስ ክቡር ሚኒስትር?
  • አንተ የምታማርር ከሆነ ሌላው ምን ይበል?
  • እሱንማ ሳስበው እንደው መሬት ተከፍቶ በዋጠኝ ነው የምለው፡፡
  • ምን ሆነሃል?
  • እውነቴን ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼን ያህል ምንድነው ያማረረህ?
  • ክቡር ሚኒስትር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ አልቻልንም እኮ፡፡
  • የፖለቲካ እንቅስቃሴ ጀመርክ እንዴ?
  • ወዴት ወዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • የምን እንቅስቃሴ ነው ታዲያ?
  • ኢኮኖሚው ምንም እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡
  • አንቀሳቅሱታ ታዲያ፡፡
  • ቀልደኛ ነዎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የምን ቀልድ ነው?
  • አካላዊ እንቅስቃሴ አይደለም እኮ ያልኩዎት፡፡
  • ባይሆን አንተ ነህ ቀልደኛው፡፡
  • የምሬን ነው ክቡር ሚኒስትር፣ ሥራችን ቆሟል ማለት ይቻላል፡፡
  • ለምን?
  • ዶላር የለም፡፡
  • አሁን ይኼን ሁሉ ችግር የምታወራው ግዛኝ እንዳልልህ ነው፡፡
  • ምንድነው የምገዛዎት?
  • ትኬቱን ነዋ፡፡
  • የቱን ትኬት?
  • የእራቱን ትኬት ነዋ፡፡
  • የባለአምስት ሚሊዮን ብሩን?
  • እህሳ፡፡
  • እየቀለዱ መሆን አለበት፡፡
  • የምን ቀልድ ነው?
  • ሥራ ምንም የለም እያልኩዎት፡፡
  • ትኬቱን ከገዛህ ሥራው ይመጣል፡፡
  • እንዴት አድርጎ?
  • ይለቀቅልሃላ፡፡
  • ምኑ?
  • ዶላሩ!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ባለሥልጣን ስልክ ደወለላቸው]

  • ሰለም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት ነህ ባክህ?
  • ሥራ እንዴት ነው?
  • ይኸው ወጥረናል፡፡
  • እዛም ሆቴል ቀሩ እኮ፡፡
  • ሥራው መቼ ያስቀምጣል ብለህ ነው?
  • እሱማ አውቃለሁ፡፡
  • ከላይ ከላይ እኮ ነው የሚጨመርብኝ፡፡
  • በለውጡ እንቅልፍ የለም ተብሏል፡፡
  • ለውጡ እንዳይቀለበስ ሌት ተቀን እየሠራን ነው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ ለውጡን ለማሳለጥ የአቅሜን እየጣርኩ ነው፡፡
  • እንደዚህ እጅ ለእጅ ካልተያያዝን ረዥም ርቀት መጓዝ አንችልም፡፡
  • የኢኮኖሚው ጉዳይ ግን እያሳሰበኝ ነው፡፡
  • ምኑ ነው ያሳሰበህ?
  • ሁሉም ነገር ተቀዛቅዟል እኮ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኸው እኛም ትንሽ እናሟሙቀው ብለን እኮ ፕሮጀክቶችን ጀምረናል፡፡
  • ምን ዓይነት ፕሮጀክት?
  • ሸገርን የማስዋብ ነዋ፡፡
  • ዛሬ አደዋወሌ ስለእሱ ለማውራት ነበር፡፡
  • ስለምኑ ለማውራት?
  • ስለእራት ግብዣው ነዋ፡፡
  • ምን ልትለኝ ፈልገህ?
  • የእራት ግብዣው አስተባባሪ ኮሚቴ መሆንዎትን ሰምቻለሁ፡፡
  • ትክክል ነው፡፡
  • ያው የለውጡ ደጋፊ መሆኔን ያውቃሉ አይደል?
  • አልገባኝም?
  • አዲስ አበባችን ሁሌም የመናፈሻ ቦታዎች እንዲኖሯት እፈልግ ነበር፡፡
  • ፕሮጀክቱም ያንን ሐሳብ ለመደገፍ ነው የታቀደው እኮ፡፡
  • እንዲያው አንድ ነገር ላስቸግርዎት ነበር፡፡
  • ምንድነው የምታስቸግረኝ?
  • ይህ ታሪካዊ ግብዣ እንዲያመልጠኝ አልፈልግም፡፡
  • ምን እያልከኝ ነው?
  • አንድ ትኬት ቢሰጡኝ ብዬ ነበር፡፡
  • የእራቱን?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ዋጋው አምስት ሚሊዮን ብር መሆኑን ረሳኸው?
  • ኧረ አውቃለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ታዲያ ከየት አምጥተህ ትከፍላለህ?
  • በዱቤ እንዲሰጡኝ ነው፡፡
  • በዱቤ?
  • አዎን በዱቤ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • በዱቤስ ቢሆን ከየት አምጥተህ ትከፍለዋለህ?
  • በጥቂት ወራት እንደምከፍለው እርግጠኛ ነኝ፡፡
  • እኮ ከየት አምጥተህ?
  • በቅርቡ መሥራቴ አይቀርም፡፡
  • ምን?
  • ሙስና!

[ክቡር ሚኒስትሩ ለደላላ ወዳጃቸው ስልክ ደወሉ]

  • ሰላም ወዳጄ፡፡
  • እንዴት ነዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ጠፋህ እኮ፡፡
  • ኧረ እርስዎ ነዎት የጠፉብኝ፡፡
  • ምን ላድርግ ብለህ ነው፡፡
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ዕዳ ውስጥ ገብቼ ነዋ፡፡
  • የምን ዕዳ?
  • የቲኬት ነዋ፡፡
  • የምን ቲኬት?
  • የእራቱ ነዋ፡፡
  • ቲኬት ሸጠው ብሩን አጠፋሁት እንዳይሉኝ?
  • እሱ ቢሆን ይሻለኝ ነበር፡፡
  • ታዲያ ምን ሆኑ?
  • የሚገዛኝ አጣሁ፡፡
  • ምንም አልሸጡም፡፡
  • ከየት መጥቶ?
  • ምነው?
  • ሰው ሁሉ ችግር ነው የሚያወራው፡፡
  • ለነገሩ እንቅስቃሴ ሁሉ ተዳክሟል፡፡
  • ኧረ አንተ እንኳን አበረታታኝ፡፡
  • ምን ተሻለ ታዲያ?
  • እንድታግዘኝ ነው የደወልኩት፡፡
  • ምን ላግዝዎት?
  • ትኬቱን ሽጥልኝ፡፡
  • እርስዎን ያልገዙዎት እኔን ማን ይገዛኛል ብለው ነው?
  • አንተ እንደምትሸጠውማ እርግጠኛ ነኝ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ይታሰብልሃል፡፡
  • ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ኮሚሽን፡፡
  • ስንት ፐርሰንት
  • 10 ፐርሰንት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ብልጽግና ፈተና ሆነውብኛል ያላቸውን አምስት ተግዳሮቶች ይፋ አድርጎ የአግዙኝ ጥሪ አቀረበ

ብልፅግና በነፃነት ስም በሚፈጸም ወንጀል ምክንያት በትግሉ ያገኘውን ነፃነት...

ዋሊያዎቹ ሁለት ሚሊዮን ብር ተሸለሙ

ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ 11 ከአይቮሪኮስት፣ ማዳጋስካርና ኒጀር ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ሁለት ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት ተበረከተለት፡፡

መንግሥት ከጦርነቱ ለማገገም በመጭዎቹ አምስት ዓመታት 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል አለ

በጦርነቱ የተሳተፉ 250 ሺሕ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋምና ወደ ኅብረተሰቡ...

ለሚቀጥለው ዓመት የነዳጅ ፍጆታ ግዥ ለመፈጸም አራት ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ተባለ

ለ2016 በጀት ዓመት የነዳጅ ፍጆታ 212 ቢሊዮን ብር ወይም...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ዜጎች የተፈተኑበት የኑሮ ውድነት

በኢትዮጵያ በየጊዜው እየተባባሰ የመጣው የኑሮ ውድነት የበርካታ ዜጎችን አቅም...

በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተጠየቀ

በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎች ዘላቂነት እንዲኖራቸውና በተቀናጀ መልኩ...

ወደ ኋላ የቀረው የሠራተኞች ደኅንነት አጠባበቅ

በአበበ ፍቅር ለሠራተኞች የሚሰጠው የደኅንነት ትኩረት አናሳ በመሆኑ በርካታ ዜጎች...

ቲቢና ሥጋ ደዌን ለመከላከል ያለመ ስትራቴጂክ ዕቅድ

ኢትዮጵያ የቲቢ፣ ሥጋ ደዌና ሌሎች የሳንባ በሽታዎች ጫና ካለባቸው...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...

[የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመመካከር በሚኒስትሩ ቢሮ ተገኝተው ውይይታቸውን ጀምረዋል]

ክቡር ሚኒስትር ባላንጣዎቻችን የእኛኑ ስልት መጠቀም የጀመሩ ይመስላል። እንዴት? ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ? እስከዛሬ እኛ የምንሰጣቸውን አጀንዳ ተቀባይ ነበሩ። በዚህም በውስጣቸው ልዩነትንና አለመግባባትን መትከል ችለን ነበር። አሁን...