- Advertisement -

አንድነት ፓርቲ አዲስ አበባን ባለአደራ አካል እንዲያስተዳድራት ጠየቀ

አዲስ አበባ የሚያስተዳድራት አካል የሥራ ጊዜውን የጨረሰ በመሆኑ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ባለአደራ አስተዳደር እስከ ጠቅላላ ምርጫ ድረስ እንዲቋቋምና ይህም ተግባራዊ እንዲሆን፣ ከሌሎች የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር በጋራ በመሆን እንደሚታገል አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) አስታወቀ፡፡

‹‹አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያዊ መኖሪያና ሀብት ማፍሪያ እንጂ፣ አንዱ ብሔረሰብ ከሌላው በልጦ የተለየ ጥቅም የሚያግበሰብስበት አይደለችም፡፡ አዲስ አበባን በአንድ ማንነት ጥላ ሥር ለማድረግ የሚደረገውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በጥብቅ እንቃወማለን፤›› በማለት ፓርቲው አቋሙን አስታውቋል፡፡

ፓርቲው ይህን አቋሙን ይፋ ያደረገው ሐሙስ መጋቢት 12 ቀን 2011 ዓ.ም.፣ ‹‹ኢትዮጵያዊነትን የሚፈታተን የለውጥ ሒደት እንዳያፈርሰን ሕዝብ በአንድነት ፀንቶ መታገል አለበት፤›› በሚል ርዕስ በራስ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡

ከአዲስ አበባ በተጨማሪ አጠቃላይ የአገሪቱን ፖለቲካዊ ሁኔታ አስመልክቶ በፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ትዕግሥቱ  አወሉና በሌሎች አመራሮች በተሰጠው በዚህ መግለጫ በአገሪቱ እየተከሰቱ ስላሉ ግጭቶች፣ መፈናቀሎችና እንዲሁም የንፁኃን ዜጎች ሕይወት መጥፋትን ለመቆጣጠርና ሰላምና ደኅንነትን ለማስፈን መንግሥት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ፓርቲው ጠይቋል፡፡

አገሪቱ በለውጥ ተስፋ ውስጥ እንደሆነች የገለጸው ፓርቲው፣ ‹‹ሆኖም የኢሕአዴግ ልሂቃን አካባቢያዊ ስሜትን የበለጠ በማጠናከርና ዛሬም በለውጥ ስም የሕግ የበላይነትን ወደ ጎን በመተው ሕዝቡ በአንድነቱ የፈጠረውን ኢትዮጵያዊያነቱን ከመፈታተናቸውም በላይ፣ በሥውርና በጥቅም ሥራአጥ ወጣቶችን በማደራጀት ለግጭት በማሰማራት ድብቅ አጀንዳዎቻቸውን ሕዝባዊ ለማስመሰል የሚደረገው ጥረት ሕዝብ የተረዳው በመሆኑ፣ ተፈጥሮአዊ ማንነትን የዘረኛ ፖለቲካ ማራመጃ ሰበብ ከማድረግ ይቆጠቡ፤›› በማለት፣ በአገሪቱ እየተስተዋለ ያለውን ግጭት የሚመለከታቸው ሁሉ ታግለው መፍትሔ እንዲፈልጉለት አሳስቧል፡፡

‹‹የፖለቲካ አለመረጋጋት በአገራችን ሁሉም ክልሎች የሚስተዋል ነው፡፡ ይኼንን ተከትሎ የዜጎች መፈናቀልና ስደት በስፋት ይታያል፡፡ የዜጎች መረጋጋትና ሰላምን ማረጋገጥ ካልተቻለ ሉዓላዊ አገር ሊኖር አይችልም፡፡ ስለሆነም ኢትዮጵያን ከልብ የምትወዷት ከሆነ ኢሕአዴግም ሆነ የለውጥ ኃይሉ የፖለቲካ ቁማሩን ትቶ፣ ከሁሉም የክልል ገዥዎች ጋር ቁጭ ብሎ በአገሪቱና በዜጎች ደኅንነት ላይ የምር ተወያይቶ ሰላምን ለማረጋገጥ እንደ መንግሥት ውሳኔ መስጠት አለበት፤›› በማለት፣ በአገሪቱ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶችን፣ ስደቶችንና መፈናቀሎችን፣ የሰው ሕይወት መጥፋትን ለማስቆም መንግሥት ውሳኔ መስጠት እንዳለበት አሳስቧል፡፡

- Advertisement -

በመጨረሻም ሕዝባዊ ለውጡን ከግብ ለማድረስ መጀመርያ ከክፋትና ከድብቅ የሴራ ፖለቲካ መንፈስ በመውጣት በፍቅርና በአንድነት ተማምኖ፣ ሁሉም የየራሱን አስተዋጽኦ ማድረግ ሲችል እንደሆነ በመግለጽ፣ ‹‹በአገሬ ያገባኛል የሚል የተደራጀ ሐሳብ ያለው ሁሉ ሊሳተፍበት የሚችል የለውጥ ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ የለውጡ አካል ማድረግ ሲቻል፣ የለውጥ ሒደቱ ዓላማውን ስቶ የቡድንና የክፍፍል ምክንያት ሊሆን አይገባም፣ መታረምም አለበት፤›› በማለት፣ አሳታፊ የሆነ የፖለቲካ ፍኖተ ካርታ እንዲዘጋጅና በአገሪቱ ጉዳይ ሁሉም የበኩሉን እንዲያበረክት ሊመቻችለት እንደሚገባ መንግሥትን ጠይቋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

አይኤምኤፍ ብሔራዊ ባንክ ገለልተኛ ሆኖ እንዲሠራ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አደረገ

‹‹ማዕከላዊ ባንክ ውሳኔዎቹን በመረጃ ላይ ብቻ ተመሥርቶ ካላሳለፈ አገሪቱንም ሆነ ኢኮኖሚውን አይጠቅምም›› ክርስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የአይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ ሰላም ማስከበር እንዲሳተፍ ምክክሩ መቀጠሉ ተገለጸ

የ38ኛው አፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ከ35 በላይ መሪዎች ይታደማሉ ተብሏል የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ ምክክሩ መቀጠሉን፣ ሒደቱ በመልካም ውጤት እንደሚቋጭ...

ገንዘብ ሚኒስቴር መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያለውን የዕዳ ሽግሽግ ድርድር አይኤምኤፍ አረጋገጠ

አበዳሪዎች የክፍያ ጊዜ ለማራዘም የአገሮች ፋይናንስ አቋምን ጨምሮ የሰላም ሁኔታ እንደሚጠና ተገልጿል የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ከቡድን ሀያ አባል አገሮች የጋራ ማዕቀፍ ሥር ከተካተቱ አገሮች...

ኢሕአፓ በኮሪደር ልማት ምክንያት ሜዳ ላይ ተጣሉ ላላቸው 455 አባወራዎች መንግሥት መልስ እንዲሰጥ ጠየቀ

ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ሊወስደው እንደሚችል ገልጿል ‹‹ሕጋዊ ከሆኑ አንድም ሰው እንዲጎዳ ስለማንፈልግ እናስተናግዳቸዋለን›› የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያከናወነ ባለው የኮሪደር ፕሮጀክት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የካቢኔ አባል የሆነ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ ስልክ ደውሎላቸው ሰሞኑን በተካሄደው ድርጅታዊ ጉባዔ ዙሪያ እያወሩ ነው]

ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡ ሰላም ሰላም፣ እንዴት ነህ? ቢዘገይም እንኳን አደረስዎት ክቡር ሚኒስትር። ለምኑ? ለፓርቲዎ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ እንኳን አደረስዎት ማለቴ ነው። ቆየ እኮ ከተጠናቀቀ? አስቀድሜ ቢዘገይም ያልኩት እኮ ለዚያ ነው...

የጋዛ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የደቀነው ሥጋት

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማችና የቀድሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የፖሊሲ አማካሪያቸው ጄርድ ኩሽነር፣ ከአሥር ወራት በፊት ነበር ፍልስጤሞችን ከጋዛ አንስቶ ሌላ ቦታ ስለማስፈር በይፋ ሲናገር...

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በውክልና ለግሉ ዘርፍ ለማስተላለፍ ያቀዳቸው አገልግሎቶች

የከተማው አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን ባሳለፈው ውሳኔ የተመረጡ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን በሦስተኛ ወገን ለማሠራት የሚያስችለውን ደንብ በማፅደቅ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ታውቋል፡፡  አስተዳደሩ ደንቡን ከማጽደቁ አስቀድሞ በሦስተኛ ወገን...

የተገራ ስሜት!

እነሆ መንገድ ከስታዲዮም ወደ ጦር ኃይሎች። በጥበቃ የተገኘ ለበርካታ ዓመታት ያገለገለ ሚኒ ባስ ታክሲ ውስጥ ተሳፍረናል፡፡ ምሁር መሳይ ተሳፋሪ አጠገቡ ለተቀመጠ የዕድሜ እኩያው ማብራሪያ...

የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ አውጪዎች ችግር የት ጋ ነው ያለው?

በጌታነህ አማረ የአንድን አገር ኢኮኖሚ ችግር ለመፍታት መጀመሪያ ቁልፍ የሆነውን ነገር መረዳት በጣም ጠቃሚ  ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ቁልፍ ነገር ተብሎ የሚጠራው ‹‹ተርኒንግ ፖይንት›› ነው፡፡...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን