Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየከተማ አውቶብስ ከባለ ተሳቢ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

የከተማ አውቶብስ ከባለ ተሳቢ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

ቀን:

ማክሰኞ መጋቢት 24 ቀን ከንጋቱ 12፡30 ሰዓት ከኦሮሚያ ልዩ ዞን ጫንጮ ከተማ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ 88 ቁጥር አንበሳ የከተማ አውቶብስ፣ በተቃራኒ አቅጣጫ ይጓዝ ከነበረ ባለ ተሳቢ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ወዲያውኑ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አውቶብሱ በተጠቀሰው ሰት ሱሉልታ ከተማ ሲደርስ ከሌላ አቅጣጫ ይመጣ ከነበረ የጭነት ተሽከርካሪ ተሳቢ ጋር የተገናኙት የአስፋልት መጠምዘዣ ላይ ሲሆን፣ ሁለቱም ሲተላለፉ ተሳቢው አውቶብሱን ስለገጨው አደጋው ሊከሰት እንደቻለ፣ የሱሉልታ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አውቶብሱ በርካታ ሰዎችን ጭኖ እንደነበር የገለጹት ኃላፊዋ፣ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች መኖራቸውንም አስረድተዋል፡፡ በአቅራቢያው በሚገኙ የሕክምና ተቋማት ዕርዳታ እንደተደረገላቸውና የተወሰኑትም ወደ አዲስ አበባ መወሰዳቸውን አክለዋል፡፡

ከሞቱት ስድስት ሰዎች ውስጥ አንዱ የአውቶብሱ ሾፌር መሆኑን ጠቁመው፣ የባለ ተሳቢው ተሽከርካሪ ሾፌር እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል ብለዋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...