Sunday, June 4, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

የማኅበራዊና የኅብረተሰብዓዊ ጥያቄ ወይስ የብሔር ብሔረሰብ ጥያቄ?

‹‹እባብ ወተት ጠጥታ መርዝ ትተፋለች፣ ቅዱስ ግን መርዝ ጠጥቶ ወተት ይተፋል!››

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ!

አሁን ያለንበት ዘመን 21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ፣ ብዙ የምዕራብ አውሮፓ አገሮችና አሜሪካንም ጨምሮ፣ እንዲሁም ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ፣ ዛሬ ደግሞ ቻይና በሳይንስ አማካይነት የቴክኖሎጂን ምጥቀት በማግኘት አነሰም በዛም የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመገንባት ችለዋል። በተለይም ባለፉት አራት አሠርታት የተፈጠሩትና ገበያ ላይ የዋሉት ቴክኖሎጂዎች ቀደም ብለው ከነበሩት ቴክኖሎጂዎች ጋር ሲወዳደሩ በጥራትም ሆነ በምቾት እግ ተሽለው የሚገኙ ናቸው። የዛሬ ርባ ዓመት ገበያ ላይ የነበሩና ለፍጆታ የቀረቡ ምርቶች ዛሬ በፍም አይታዩም። እንዲሁም ቴክኖሎጂዎች እጅግ ከመሻሻላቸው የተነሳ በተወሰነ ሰዓትና የሰው ኃይል ብዙ ምርቶችን ማምረት የሚቻልበት ወቅት ውስጥ ነው የምንገኘው። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ መኪናንና የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች በግማሽ ወይም በሙሉ አውቶማቲክ ወይም ሮቦ እየታገዙ ነው የተለያዩ ክፍሎችን የሚገጣጥሙትና ወደ አንድ ወጥ ምርትነት የሚለውጡት።

ስለሆነም በዚህ የቴክኖሎጂ ዓለም በመታገዝ እኛም በብዙ ሺ ማይልስ የሚቆጠር ርቀትን አልፈን መጥተን አውሮፓና አሜሪካ፣ እንዲሁም ሌላ ለጠነ የሚባለው ዓለም ውስጥ ተበታትነንና ተደላድለን በመኖር የቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚዎች ለመሆን በቅተናል። አዳዲስ መኪናዎችን የምናሽከረክር፣ በኢንተርኔት ዓለም ውስጥ በመኖር ኢንፎርሜሽኖችን አንድ ደቂቃ በማይፈጅ ጊዜ ውስጥ የመለዋወጥ ድል አለን። የምንኖርበት ቤትም ማንኛውንም ነገር ያሟላ ነው። እነዚህ ሁሉ ቴክኖሎጂዎች የተገኙት ዝም ተብለው አይደለም ወይም ከሰማይ ዱብ ብለው የወረዱ አይደሉም። ከፍተኛ ምርምርንና ሙከራን በማድረግ ነው ቴክኖሎጂዎቹ የተገኙት። የጥቂት አገሮችና ዝቦች የራ ውጤቶች በመሆን ከእነሱ አልፈው የዓለም ማበረሰብ እንዲጠቀምበት አድርገዋል። እስቲ እናስብ የአውሮፓ አገሮችና ሌሎችም የሃይቴክ ባለቤት የሆኑ አገሮች ድሜያቸውን በሙሉ የሚሆን የማይሆን ነገር አንስተው ቢጨቃጨቁ ኖሮ እንደዚህ ዓይነቱን የቴክኖሎጂ ምጥቀት ማየት ይችሉ ነበር ወይ? በፍጹም! አንድም ርምጃ ወደ ፊት መራመድ ባልቻሉም ነበር። የእነሱ ጣ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው የዓለም ዝብም ጣ የጨለማና የድህነት ኑሮ በሆነ ነበር። እንደኛው በድህነትና በረሃብ እንዲሁም በደት በማቀቁ ነበር።

ወደ እኛ አገር ስንመጣ፣ ምናልባት ከዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት የተነሳ የብረሰብ ችግርና ጭቆና የሚሉት ነገር ጭንቅላታችንን ወጥሮት ዛሬም እንደ አዲስ አጀንዳ ይዘን ስንጨቃጨቅ እንገኛለን። ዋናው ችግራችንና የልጣኔውም ቁልፍ እሱን በመፍታት ብቻ ይገኝ ይመስል፣ ብሬ ተበደለ፣ ተጨቆነ፣ ተናቀ፣ አማርኛን ተገድጄ ነው የተማርኩት፣ መለያዬን እንደገና መልሼ ማግኘት አለብኝ በማለት ያልተወራረደ ሳብ ያለን ይመስል በዚህና ሌሎች እልክ አስጨራሽና፣ የሰውን ጭንቅላት ወጥረው በሚይዙ፣ ግን ደግሞ የአንድን ኅብረተሰብ ችግር ለመፍታት በማይችሉ ነገሮች ላይ ስንጨቃጨቅና ሰሚናርም ስናዘጋጅ እንታያለን። ይህንን ያረጀና በታሪክ ውስጥ ካለማወቅ የተነሳ የተደረጉ ስህተቶችን እየደጋገምን በማንሳት የታዳጊውን ትውልድ ጭንቅላት በርዘናል። ለማቲማቲክስ፣ ለፊዚክስ፣ ለኬሚስትሪ፣ ለባዮሎጂና፣ እንዲሁም ለሌሎች የዝባችንና የአገራችንን ችግሮች መፍቻ በሆኑ ቴክኖሎጂዎች ላይ ከመረባረብ ይልቅ የብር ጥያቄ የሚሉትን የቅኝ ገዢዎችን የመከፋፈያ አስተሳሰብ የራሳችን በማድረግ ሃምሳ ዓመት ያህል እርስ በርሳችን ተከሳክሰናል። ጦርነት ከፍተን በብዙ መቶ ሺ የሚቆጠር ወንድሞቻችንና እህቶቻችን እንዲያልቁ አድርገናል። ከፍተኛ የታሪክና የባህል ወንጀል ርተናል።

የዛሬው የአገራችን ሁኔታ እንዳለ ሆኖ፣ ዝባችንም የመረረ ትግል በሚያደርግበት ወቅት አንዳንዶች የትግሉን አቅጣጫ ለማዘናጋት የብረሰብን አጀንዳ እንደዋና የችግሩ ምንጭ አድርገው በማንሳት ወጣቱን በስሜት እየቀሰቀሱትና የማሰብ ኃይሉን ችግርን በማይፈታ ነገር ላይ እንዲያተኩር በማድረግ ላይ ናቸው። እንደሚታወቀው፣ በተለይም ኋላቀሩ በሚባሉ አገሮች ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮችና በዝብ ላይ በተለያየ መልክ የሚደርሱ ጭቆናዎች አብዛኛውን ጊዜ ካለማወቅ የተነሳ ነው። ኅብረተሰብዊ ተሃድሶ በሌለበትና ብዙ ነገሮች በዘልማድ በሚሩበት አገሮች ውስጥ ልጣንን የጨበጡ ኃይሎች የአንድ ዝብ ኑሮ መሻሻልና ነፃ መውጣት ጉዳይ እስከዚህም ድረስ የሚታያቸው አይደለም። እስከ 1966 ዓ.ም. ድረስ የነበረው የአገራችን አስተሳሰብ ይህንን ይመስል ነበር ብሎ ከሞላ ጎደል መናገር ይቻላል። ከዚህ ስነነሳ ቀደም ብለው የተነሱት የመደብና የብረሰብ ጥያቄዎች የአገራችንን መረታዊ ችግሮች ያላገናዘቡ፣ የይንን መረተ ሳብ ያልተከተሉ፣ በተለይም በጭንቅላት ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶችን ያላወጡና ያላወረዱ ነበሩ። በመሆኑም ዛሬም እንደትላንትናው ከዚህ ይነቱ አስተሳሰብ ባለመላቀቅ ያለንበትን ሁኔታ በመረዳትና ትግላችንን በሳብ ዙሪያ አሰባስበን ከመታገል ይልቅ ጊዜው እንዳያመልጠን በማለት ኃይልን በሚበታትንና የአገራችንንም ችግር በማይፈታ ላይ እንረባረባለን። የ27 ዓመቱ የአንድ ብር ኃያልነት የሰፈነበት የጭፍጨፋና የዘረፋ ዘመን አለፈ ስንልና ደስታችንን ሳናጣጥመው፣ ጊዜው የኛ ነው ብለው በተነሱ፣ የታሪክን ኃላፊነት ባልተገነዘቡና ሞራላዊ ግዴታ በማይሰማቸው ኃይሎች አገራችንና ዝባችን ወደማይሆን አቅጣጫ እንዲያመሩ እየተደረገ ነው። መረታዊ በሆኑ የኢኮኖሚና የማበራዊ ጉዳዮች ላይ፣ ማለትም ድህነትን መቅረፍ፣ የራ መስክን መክፈትና ለወጣቱም የሙያ ልጠና ከማቋቋምና አገራችንን በፀና መረት ላይ ከመገንባት ይልቅ አሁንም እንደትላንትናው የተያዘው ፈሊጥ በዚህም በዚያም ብሎ የአንድ ብረሰብ የበላይነት ማስፈን ነው። ይህ ይነቱ አካሄድ ደግሞ ያለውን ችግር የሚፈታ ሳይሆን የሚያባብሰውና ለአዲስ የወንድማማቾች ጦርነት የሚጋብዘን ነው። ፖለቲካ ሳይሆን ተራ ሽወዳና አገራችን በውጭ ኃይሎች እንድትወረር  የሚያደርግ አደገኛ አካሄድ ነው።

ይህንን መረት በማድረግ በምንም ይነት የአንድን ኅብረተሰብ ችግር መፍታት የማይችለውን የብረሰብ ጥያቄ እየተባለ የሚወተወተውን ኢይንሳዊ ጽንሰ ሳብ ለማሳየት እሞክራለሁ። ከዚህም በመነሳት የአንድ ዝብ መረታዊ ችግሮችና አትኩሮዎች የማበረሰባዊ ችግሮች (The Social Question) መሆናቸውን ለማረጋገጥ እሞክራለሁ።

ለመሆኑ ብር የሚባል ነገር አለ ወይ?

በመጀመሪያ አንድ ሰው ከዚህኛው ወይም ከዚያኛው ብረሰብ ከሚባለው ክፍል መወለዱ ተፈልጎና ተመርጦ አይደለም። አንድ ሰው እንደ ሰው ሆኖ ነው የሚወለደው እንጂ እንደ ብረሰብ ሆኖ አይደለም የሚወለደው። ስለሆነም የአንድ ሰው መለኪያው ልክ እንደማንኛውም ሌላ ሰው ሰው መሆኑን የሚያረጋግጡ አካልና ልዩ ልዩ ባሕሪዎችን ያዘለው አዕምሮ ሲኖሩት ብቻ ነው። ሁለተኛ፣ የሰው ልጅ ውስጠ ኃይል ስላለው አንድ ቦታ ረግቶ ስለማይኖር ወደ ሌላ ቦታ ሄዶ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል ጋር በመጋባት ልጆች ይወልዳል። በዚህም የተነሳ በተለያዩ ብረሰብ እየተባሉ በሚጠሩ የሰው ልጆች ዘንድ በመጋባት የተነሳ አንድ ወጥ ባህል ሳይሆን ከተለያዩ ብረሰቦች ተጨምቆ የሚወጣ ባህል የሚሉት ነገርና በአንድ ግዛት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን የሚያግባባ ቋን ይፈጠራል። በሌላ አነገጋር፣ በአንድ አገር ውስጥ የተለያዩ ብረሰብ እየተባሉ የሚጠሩ ሰዎች ቢኖሩም ይህም ማለት በንጹ መልክ አንተ ኦሮሞ ነህ፣ አንተኛው ደግሞ አማራ ነህ፣ አንቺ ከፍቾ ነሽ እያሉ መናገር በፍም አይቻልም። አንድ ሰው የአንድን ብረሰብ ቋንቋ አቀላጥፎ በመናገሩ ብቻ አማራ ነው ወይም ኦሮሞ ነው የሚያስብለው አንዳች ነገር ሊኖር አይችልም። ስለሆነም አንደኛው አንድ አካባቢ በመወለዱና በማደጉ ብቻ አማራ፣ ጉራጌ ወይም የም ወይም ሌላ እየተባለ እየተፈረጀበት፣ ከሌላው እሱን መሰል ከሆነው በእግዚአብር አምሳል ሆኖ ከተፈጠረው ወንድሙ ወይም እህቱ ጋር የሚያጣላው ምንም ምክንያት የለም። በስተኛ ደረጃ፣ ከላይ እንዳልኩት የሰው ልጅ ውስጣዊ ኃይል ስላለውና አዳዲስ ነገሮችን በመፍጠርና በንግድ አማካይነት በመለዋወጥ እርስ በርሱ ስለሚገናኝ በአንድ አካባቢ የሚኖር ብረሰብ በዚያው ሁኔታ መቶና ሁለት መቶ ዓመታት ሊቆይ በፍጹም አይችልም። በ ክፍፍልና በንግድ አማካይነት በሚፈጥረው ግንኙነት በመዋለድና በመጋባት ብረሰብ የሚባለው ነገር እየከሰመ ይሄዳል። ስለዚህም በዛሬው በ21ኛው ክፍለ ዘመን በአንድ አገር ውስጥ የሚኖርን ዝብ በብሔረሰብ በመከፋፈልና በመቁር ይኸኛው የዚህ ብረሰብ አካል ነው፣ ሌላው ደግሞ የዚያኛው አካል ነው እያሉ መጥራት በፍም አይቻልም።

ወደ ታሪካዊ ሁኔታዎች ስንመጣና የአገራችንን ሁኔታ ስንመረምር፣ በተለይም ከአንደኛው ብረሰብ የተውጣጡ የገዢ መደቦች፣ ለመስፋፋት ሲሉ በሃይማኖትና እንዲያም ሲል በጦርነት አንዳንድ ግዛቶችን በመያዝና በቁጥጥራቸው ስር ካደረጓቸው የገዢ መደቦች ጋር በመጋባት ልዩ ይነት ኅብረተሰብዊ እርታን ሊሰጡ ችለዋል። ስለሆነም አማራዎችን ይወክላል የሚባለው የገዢ መደብ14ኛው ክፍለ ዘመን በመጀመሪያ ግዛቱን ለማስፋፋት ሲል አስተማሪዎች በደቡቡ ክፍል በማሰማራት የክርስትናን ሃይማኖት በማስተማርና እዚያ ካሉት ብረሰብ ተብለው ከሚጠሩት ጋር በመጋባት በአካባቢው ልዩ ዓይነት ባህል ሊስፋፋና ሊዳብር ችሏል። በመሆኑም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ግዛትና የደቡቡን ክፍል በሚገዙት አምስት ንጉዊ አገዛዞች መከል የጠበቀ ግንኙነት እንደነበር ታሪክ ያረጋግጣል። ይህ እንግዲህ ኦሮሞዎች ዛሬ ኦሮሚያ እያሉ የሚጠሩትን ግዛት ከመውረራቸው በፊት ነው። በሌላ ወገን ደግሞ ኦሮሞዎች ከአንድ አካባቢ በመነሳትና ቀስ በቀስ አምስቱን የደቡን ንጉዊ አገዛዞች በመደምሰስ የራሳቸውን ግዛቶች ይመርታሉ። ቀድሞ የነበሩ የከተማና የመንደሮችን ስሞች በመቀየር ሌላ የኦሮምኛ መጠሪያ ስም ይሰጧቸዋል።  ቀስ በቀስም  ከከብት አርቢነት ወደ ተቀማጭ አራሽነትና መሬትንም በመቆጣጠር የገዢ መደብ ባሕሪን ያዳብራሉ። ወደ ሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ሲያመሩ ደግሞ በዚያ አካባቢ ብዙ ጉዳት ካደረሱና ብዙ ዝብ ለኅልፈት ከዳረጉ በኋላ ቀሰ በቀስ ከተቀረው የኅብረተሰብ ክፍል ጋር በመጋባት እዚያ ለነበረው ባህል ልዩ እርታን ይሰጡታል። ወደ ገዢ መደብነትም በመቀየር ታሪክን ሪ ለመሆን ችለዋል። በሌላ አነጋገር፣ ልክ እንደ ሌሎች አገሮች መዋጥና መዋዋጥ እንዳለ ሁሉና፣ አንደኛው ሌላውን አሸንፎ አንድ ትልቅ አገር ለመግዛት እንደሚፈልግ ሁሉ ይህም ይነቱ ታሪካዊ ግዴታና ድርጊት በኛ አገርም ተካሂዷል። የሚያሳዝነው ግን ከዚህ ብረሰብ ብቻ ነው የፈለቅነው የሚሉ ግለሰቦች የራሳቸው ብረሰብ ሲስፋፋ ያደረሰውን በደልና ዝርፊያ ወደ ጎን በመተው እነሱ ብቻ ተጎጂዎች የሆኑ በማስመሰልና በማውራት ታሪክን በማጣመምና የማይሆን ነገር በማውራት ሰውን ለማሳመን ሲሞክሩ ስናይ እነዚህ ሰዎች የቱን ያህል የታሪክ ደትና የኅብረተሰብ ዕድገት ያልገባቸው መሆኑን እንመለከታለን።

20ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በአገራችን ምድር አዲስ የተፈጠረው ኅብረተሰብዊ ግንኙነት ከካፒታሊዚም ጋር በጥብቅ የሚገናኝና የሚተሳሰር ነው። ውስን በሆነ መልክ የገባው ካፒታሊዝም የተወሰነ የኅብረተሰብ ግንኙነት እንዲፈጠር ቢያደርግም፣ በሌላ ወገን ደግሞ ባልተስተካከለ ዕድገት ምክንያት የተነሳ በአንድ አካባቢ የሚኖር የኅብረተሰብ ክፍል ብቻ ሳይሆን ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የኅብረተሰብ ክፍል በድህነት ውስጥ የሚኖር ነበር። ይሁንና ግን ይህ ይነቱ ያልተስተካከለ ዕድገት ከተሳተ የዘመናዊነት (modernization) አገባብና ደት ጋር የተያያዘ መሆኑ ቀርቶ የብረሰብ ጭቆናና የመደብ ችግር ተብሎ በመወሰዱ እንደዚህ ዓይነት የተሳተ ምሁራዊ ግንዛቤ አሉታዊ ኃይል (Negative Energy) ያላቸው ኃይሎች ብቅ እንዲሉና አለመረጋጋት እንዲኖርና፣ በተለይም በተወሰኑ አካባቢዎች ጦርነት እንዲስፋፋ በማድረግ የአገሪቱን አንድነትና ቀስ ብሎ በጥገናዊ መልክ ሊስተካከል የሚችለውን ሁኔታ መፈታተን ጀመሩ። እንደ አንዳንድ አገሮች ለጥገናዊ ለውጥ ከመታገልና ሰፋ ያለ ምሁራዊ ዕውቀት ከማዳበር ይልቅ በጊዜው የነበረውን ጭቆና የሚባለውን ነገር በጦርነት ብቻ ነው ማሸነፍ የሚቻለው በማለት አገራችንን ወደ ተወሳሰበና በቀላሉ ሊፈታ ወደ ማይችል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ከተቷት። ረጋ ካለና ጥልቅነት ካለው ምሁራዊ ጥናትና ውይይት ይልቅ በተወሰኑ ነገሮች ላይ ብቻ በማኮር ማበራዊና ኅብረተሰብዊ፣ እንዲሁም የይንስና የቴክኖሎጂ አጀንዳዎች ትኩረት እንዳይሰጣቸው አደረጉ። የኢትዮጵያ ዋናው ችግር አገሪቱ ‹‹የብረሰቦች እስር ቤት›› በመሆኗ ነው የሚለውን ኢይንሳዊና ምሁራዊነት የሌለውን የተረት ተረት በማስፋፋት አንድ ዝብ ታሪክን እንዳይራ አገዱት። በተለይም ወያኔ ልጣንን በበላይነት በሚቆጣጠርበት ዘመን ለብዙ ዘመናት ልጣን ላይ ለመቆየት ሲል ይጠቀምበት የነበረው ፖሊሲ የብረሰብን ጥያቄ  ዋናው የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ መሪያ በማድረግ ነበር። ከሞላ ጎደል ወያኔ ከልጣን ከተወገደ በኋላ ደግሞ የዝባችንን ዕውነተኛ የነፃነትና የሥልጣኔ ጥም የተገነዘቡ ኃይሎች ፍላጎቱን ለማዳፈንና የጨለማውን ዘመን ለማርዘም ማንም ሳይመርጣቸው የኦሮሞ ብረሰብ ተጠሪ ነን በማለት ፖለቲካውን በመጥለፍና (Highjack) ለራሳቸው የአጭር ጊዜ መጠቀሚያ በማድረግ በወንድማማች ዝብ መከል መተማመን እንዳይኖርና የመጨረሻ መጨረሻ በውጭ ኃይል የሚደገፍ ታዊ አገዛዝ ለማስፈን ደፋ ቀና ሲሉ ይታያሉ። ወጣቱን ያሳስታሉ። እንደፈለጋቸውም በመውጣትና በመግባት ቅስቀሳ በማድረግ የፖለቲካውን አየር ሊበርዙት ችለዋል። እንዲከፍቱ በተፈቀደላቸው የዜና ማራጫ አማካይነት ይንሳዊና ፍልስፍናዊ መረት የሌለው ዜና አይሉት ነገር በማናፈስ ዝባዊ ዕልቂት እንዲፈጠር በማድረግ ላይ ናቸው። ለዚህ ድርጊታቸው ደግሞ የኢትዮጵያዊነትን ርማ የለበሱ የዜና ማራጫዎች እየተባበሯቸው ነው። በዚህ አካሄዳቸው ግን እንታገልለታለን የሚሉትን ብረሰባቸውንም በፍጹም አይጠቅሙትም። የድህነቱንና የኋላቀርነቱን ዘመን ከማራዘም በስተቀር ምንም ፋይዳ ሊሩ አይችሉም። የሚፈልጉትንም ነፃነት ሊቀዳጁም በፍጹም አይችሉም።

የአገራችን ችግር ማበራዊና ኋላቀርነት እንጂ የብረሰብ ጥያቄ አይደለም!  

ለፉትን ስድሳ ዓመታት የአገራችንን የመንግት አወቃቀርና ከዚህ የሚመነጨውን ፖሊሲ ለተከታተለ፣ ስቱም አገዛዞች በሳይንስ የተጠና፣ ፍልስፍናንና ንድፈ ሐሳብን (ቲዎሪን)ረት ያደረገ፣ አገራችንን የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት ሊያደርጋት የሚችል ፖሊሲ እንዳልነበራቸው መገንዘብ ይቻላል። ስለሆነም ዝባችን ኋላቀር ከሆነ የአኗኗር ስልት ተላቆ ምርታማነትን በማሳደግና ኑሮውን አሻሽሎ ሰፋ ያለና ጠንራ ኅብረተሰብ እንዲመርትና ተከታታይነት እንዲኖረው የወሰዱት ሳይንሳዊ ፖሊሲ በፍጹም አልነበረም። የአገራችንን ሁኔታና የዝባችንን ፍላጎት ያላገናዘበና፣ የተከታዩንም ትውልድ ዕድል ቁጥር ውስጥ ያላስገባ፣ በውጭ ኃይሎች የተነደፈና ተግባራዊ ያደረጉት ፖሊሲ በአገራችን ምድር በይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመረተ ኅብረተሰብዊ ሀብት እንዳይፈጠር ለማድረግ በቅቷል። በ20ኛውና 21ኛው ክፍለ ዘመኖች በአገራችን ምድር ልጣንን የጨበጡ የገዢ መደቦች አገራችን ያላትን ተፈጥሮአዊ ሀብት በ ርዓት መጠቀም ስላልቻሉና ውነተኛ የሆነ ብራዊ ሀብት ሊፈጥር የማይችል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረጋቸው በጠቅላላው አገሪቱ ውስጥ የተስተካከለ ዕድገት እንዳይፈጠር አድርገዋል። ከተች እንዳይገነቡ፣ ሰፊው ዝብ በተለያየ ሙያ በመልጠን፣ በንግድ አማካይነት እንዳይተሳሰርና እንደ አንድ ዝብ ታሪክን እንዳይራ በአብዛኛው ጎኑ ሳያውቁት ከፍተኛ መሰናክል ሊፈጥሩ ችለዋል። ስለሆነም ድህነትን ለመቅረፍ ቀን ከሌሊት ደፋ የማይል አገዛዝ በመረቱ ጥሎ የሚያልፈው ያልተረጋጋና በሆነው ባልሆነው የሚናቆር ሕዝብ እንደሆነ የአንዳንድ አገሮችም ታሪክ ያስተምረናል። እንደዚህ ዐይነቱ በሰፊ የኢኮኖሚና የማበረሰብዊ መረት ላይ ያልተገነባ አገር ደግሞ መጥፎ ህልም ለሚያልሙ ጥራዝ ነቅ ለሆኑ የውስጥ ኃይሎችና፣ የአገራችንን መዳከምና እንዲያም ሲል መበታተን ለሚፈልጉ ኃይሎች ቀዳዳ መስጠቱ የማይቀር ጉዳይ ነው።

ስለሆነም ባለፉት ሃምሳ ዓመታት የብረሰብን ጥያቄ አንግቦ ነፃ እወጣለሁ በማለት እዚህና እዚያ የሚሯሯጠው ኢትዮጵያዊ ኃይል በሙሉ በዝባችንና በአገራችን ላይ ጦርነት አውጇል። በውጭ የስለላ ኃይሎችና በአካባቢው በሚገኙ የአገራችንን መጠናከርና መረጋጋት በማይፈልጉ አጎራባች አገሮች በመታገዝ አገራችንና ዝባችን በቀላሉ ሊወጡ የማይችሉት ችግር ውስጥ ከቷቸዋል። እነዚህ ለነፃነታችን እንታገላለን የሚሉ ኃይሎች በራሳቸው ላይ አጉል ዝቅተኛ ስሜት በማሳደርና፣ ወጣቱን በመቀስቀስና አመፀኛ እንዲሆን በማድረግ እንዳየነውና እንደቀመስነው ለብዙ መቶ ሺ የሚቆጠር ሰው ይወት መጥፋትና፣ አገራችንም አሁን ባለችበት ሁኔታ እንድትገኝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። ‹‹በቡሃ ላይ  ጆሮ ደግፍ›› ተጨምሮበት እንደሚሉት አነጋገር፣ ሌሎችም ከብረሰብ ጋር ያልተያያዙ ኃይሎች በዚህና በዚያኛው ሙያ የተሰማሩ የአገራችን ምሁሮች ከሲቪሉም ሆነ ከወታደሩም የተውጣጡ የውጭ የስለላ ኃይሎች የሚሰጧቸውን ምክርና የገንዘብ ድጋፍ ተገን በማድረግ አገራችንን እንደነቀርሳ በሽታ ሰርስረዋታል፡፡ በፊዳላዊ ተንኮል ክፉኛ አዳክመዋታል። እነዚህ ኃይሎች በተለይም  ቀደም  ብለው ከነበሩት የገዢው መደቦች ጋር በጥብቅ የተሳሰሩና ዝምድናም የነበራቸው ሲሆኑ፣ ዋናው ዓላማቸው በተለይም አገራችንና ዝባችን የይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት በመሆን ጠንካራ አገር እንዳይመርቱ ማድረግ ነው። በዚህ ይነቱ የአንድን አገር ህልውና የሚያወድምና ተከታታዩ ትውልድም በየጊዜው አዳዲስ ታሪክ እንዳይራ የማርክሲዝምን ርማ አንግቦ እታገላለሁ ይል የነበረው ኃይል በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የአገራችንን ውድቀት አፋጥኗል ማለት ይቻላል።

ወደ ዋናው ቁም ነገር ስንመለስ፣ በተለይም እንደነ ጃዋር የመሳሰሉት አዳዲስ የፖለቲካ ተዋናይ ነን ብለው የፖለቲካን ትርጉም ሳይረዱ የተሰጣቸውን የሚዲያ ዕድል በመጠቀም የሚያስፋፉት ቅጥ ያጣና የተዘበራረቀ ልፍለፋ የፖለቲካውን ትግል እየረበሸውና አብዛኛውን ሕዝብ ደግሞ ግራ እያጋባው እንደመጣ እንመለከታለን። ዝባችን በፍርሃት በመዋጥ ፈጣሪን እየለመነ እንዲኖር አድርገውታል። በመተባበርና በመከባበር አንድ ለሁሉም የምትሆን ነፃ አገር እንዳገነባ አለመተማመንን አስፋፍተዋል። ጃዋርና ተከታዮችም ሆነ በዳውድ የሚመራው የኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅት ‹‹ተጨቁነናል፣ ነፃነታችንንም መልሰን ማግኘት አለብን›› የሚለውን ከማራገብና ሕዝብን ከማወናበድ በስተቀር፣ ይህ ነው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማበራዊ ፖሊሲያችን ብለው ሲያስተምሩና ሲከራከሩ በፍጹም አይታዩም። በመረቱ ሳይንስን፣ ፍልስፍናንና ቲዎሪን መረት አድርጎ የማይካሄድ ትግል ወደ ፋሺዝም ነው የሚያመራን። እንዳየነውና በታሪክም እንደተረጋገጠው በብረሰብ ላይ የተመረኮዘ ናሺናሊዝም ከሌላው የተለየሁኝ ነው ብሎ ስለሚያምን ነፃነቱን ሊቀዳጅ የሚችለው እሱን እንዳለ በመግደል ወይም በመጨረስ ብቻ ነው። ይህም ማለት ሂትለር የመጨረሻው መፍት(The final Solution) በአገራችንም ምድርም ተግባራዊ የማይሆንበት ምክንያት የለም። ወያኔም እስከተቻለው ድረስ ይህንን ይነቱን አንድን ብሔረሰብ የማውደም ፖለቲካ ሲከተል ነበር። የአሁኖቹም ጽንፈኞች ይህንን ከማድረግ አይቆጠቡም። በየቦታው የሚካሄደው መፈናቀልና መሰደድ ይህንን ነው የሚያረጋግጠው። ሂትለር ለጀርመን ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉትን ይሁዎችን በመጥላትና ዝቅተኛ ስሜትም ስላደረበት ነው ዘመቻ ያደረገባቸውና የመጨረሻ መጨረሻም ለስድስት ሚሊዮን ሰዎች ማለቅ ምክንያት የሆነውና ሆሎኮስት የሚባለውን ዘግናኝ ድርጊት የፈጸመው። እነ ሻቢያና ት የሚባሉትም ገዢዎች በአጀማመራቸው የማርክሲዝምን ርማ ይዘው ቢነሱም ዋናው ዓላማቸው የአማራውን ሕዝብ ቅስም ለመስበርና እነሱ በጭንቅላታቸው ውስጥ የቀረጹትን የአማራውንና የኦርቶዶክስን ሃይማኖት የበላይነት ማዳከምና የራሳቸውን የበላይነት ለማረጋገጥ ነበር። ድርጊታቸው ከፋሺዝም የሚያንስ አይደለም ማለት ነው።

በአገራችን ምድር ውስጥ እስካሁን ድረስ የተካሄዱት ትግሎች በሙሉ ራሳችንን የሚያዳክሙ እንጂ ለማንም የሚጠቅሙ አይደሉም። የታሪክን ደትና የኅብረተሰብን ዕድገት፣ ከዚህም በላይ ደግሞ በአንድ አገር ውስጥ ያለን ምሁራዊ ድክመትና፣ ጠለቅና ሰፋ ያለ ምሁራዊ እንቅስቃሴ አለመኖር ያላገናዘቡ በመሆናቸው እርስ በእርሳችን እንድንፋተግ ተደርገናል። የድንቁርናችን ሰለባ በመሆን ተባብረንና ተቻችለን ታሪክን ከመራት ይልቅ የውጭ ኃይሎች ተጠሪና ተመካሪ በመሆን የአገራችንን ውድቀትና መበታተን እያፋጠን እንገኛለን። የተማርነው ትምህርት ሁሉ ጭንቅላታችንን አንጾት የተቀደሰ ተግባር ከመራት ይልቅ መጥፎ ነገር የተማርን ይመስል በክፉኛ መቀናናትና መጠላላት በመወጠር መራት ያለብንን ነገር እንዳንራ ታግደናል። ይህ ይነቱ ታሪክን ያላገናዘበ ትግል ግን አንድ ቦታ ላይ መገታት አለበት። እያንዳንዱ ምሁር ራሱን በራሱ በማግኘት ታሪክ ሪነቱንም የሚያረጋግጥ መሆን አለበት እንጂ የአገራችንን ውድቀት ለማፋጠን ከውጭ ኃይሎች ጋር መራት የለብትም። እርስ በርስ መመካከርና ሳብ ለሳብ መለዋወጥ እንጂ ከውጭ ኃይሎች ምንም ዓይነት ምክር የሚጠይቅበት ምክንያት የለውም።

‹‹የኦሮሚያን ሪፐብሊክ›› እንመርታለን ብለው ደፋ ቀና ለሚሉት ኃይሎች የመጨረሻ ጥሪዬ፣ በኢትዮጵያ ምድር ታሪክን ልትሩ የምትችሉት በዚህ ይነቱ አካሄድ ሳይሆን፣ ከሌላው ወንድሞቻችሁና እህቶቻችሁ ጋር በመመካከርና ሳብ ለሳብ በመለዋወጥ ብቻ ነው። ዓላማችንም ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የሚስማና፣ ተደላድሎና ተከባብሮ ለመኖር የሚያስችለውን አገር መገንባት ብቻ ነው። ስለሆነም የብሔረሰብና የሃይማኖት ጥያቄዎች የኅብረተሰብ ችግሮችን ሊፈቱ የሚችሉ አይደሉም። የአንድ ኅብረተሰብ ችግር በሳይንስና በቴክኖሎጂ አማካይነት ብቻ ነው ሊፈታ የሚችለው። የንጹህ ው ጉዳይ፣ የተመጣጠነ ምግብ፣ በደንብ የተራ መጠለያ፣ ክምናና ጭንቅላትን ክፍት የሚያደርግና፣ ሰው መሆናችንን እንድንገነዘብ የሚያደርገው ሁለገብ ትምህርት የጠቅላላው ሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄዎች ናቸው። እነዚህን ለመሳሰሉት ጥያቄዎችና የሕዝብ ፍላጎቶች መልስ መስጠት የምንችለው በተናጠል በመታገልና የራሴ አጀንዳ አለኝ በማለት ሳይሆን፣ በአንድ የአስተሳሰብ ዙሪያ ስንሰባሰብ ብቻ ነው። ዛሬ ለጠኑ የሚባሉ አገሮች ቀናውን መንገድ በመከተልና በመደማመጥ ብቻ ነው ለማደግና ዓለምን በይንስና በቴክኖሎጂ ለመቆጣጠር የቻሉት። ስለዚህም ወዲህና ወዲያ ከምንሯሯጥ ይልቅ እስቲ አንድ ጊዜ ተምጠን የምንራውን ራ ሁሉ እናሰላስል። አስተሳሰባችንን በሙሉ በሳይንስና በቴክኖሎጂ፣ እንዲሁም በፍልስፍና ዙሪያ እናድርገው። ለብሔረሰብ ሳይሆን ለነዚህ ነገሮች ቅድሚያ እንስጣቸው።

የዛሬውን የዶ/ር ዓብይን አገዛዝ የማሳስበው ውስጥ ሆነው አደገኛ ፖለቲካ ጨዋታ የሚጫቱ ግለሰቦችን መግታት አለባቸው። ፖለቲካቸው ጠቅላላውን ሕዝብ የሚመለከትና ኃይሉንም የሚሰበስብ መሆን አለበት። ለዚህ ደግሞ የውስጥ ፖለቲካ ተብሎ የሚጠራና አንድን ሕዝብ እንደማበረሰብ የሚያሰባስበውና የሚያጠናክረው ሰፋ ያለ ፖሊሲ አለ። የዚህም ፖሊሲ ፍልስፍናዊ መረት ጠቅላላው ሕዝብ ከየት እንደመጣ፣ ለምን እንደሚኖር፣ ምን ማድረግ እንዳለበትና ወዴትስ እንደሚጓዝ የሚያስገነዝበው ነው። ይህንን ለማረጋገጥና በጠንካራ መረት ላይ ለመገንባት ደግሞ በይንስና በፍልስፍና የተፈተነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ መሆን አለበት። በሌላ አነጋገር፣ ብራዊ ሀብትን የሚፈጥር የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ መሆን አለበት። እንደማየውና እንደምከታተለው ከሆነ አሁንም አገዛዙ የውጭ ምክርንና ትዕዛዝን በመቀበል ነው ወደፊት ለመጓዝ የሚጥረው። በተለይም እየደጋገሙ የገንዘብ ቅነሳ ማድረግና በገበያ ስም የተካሄደውና የሚካሄደው ፖሊሲ አገሪቱን የባሰ ደሃ ነው ያደረጋት፡፡ ዝባችንን በኑሮ ውድነት እንዲማረር አድርጎታል። ስለሆነም አገዛዙ ከቻይናዎችና ከሩሲያዎች እንዲሁም ከደቡብ ኮሪያ መንግታት መማር አለበት። በራስና በሕዝብ ላይ መተማመን ብቻ ነው አንድን ሕዝብ ነፃና የተከበረ ሊያደርገው የሚችለው። ከዚህ ስንነሳ በተለይም ከረብ መንግታት ጋር ያለው ግንኙነት በጥብቅ መታሰብ ያለበት ጉዳይ ነው። ውስጥ ለውስጥ የሚካሄድ ሳይሆን ለውይይትና ለክርክር መቅረብ አለበት። የአገራችን ጉዳይ የመንግት ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ዝባችንም ጉዳይ ስለሆነ አጠቃላዩ የውጭ ፖሊሲያችን ወይም ፖለቲካችን ሕዝብ ሳያውቀው በዝግ ችሎት የሚካሄድ መሆን የለበትም። በዚህ ዓይነት ፖለቲካ ብራዊ ነፃነታችን መደፈሩ ብቻ ሳይሆን ባላዊ አገር እንዳንገነባ እንታገዳለን። መልካም ግንዛቤ!!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

Previous article
Next article
spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles