Wednesday, March 22, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላው ጋር እያወሩ ነው

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ታዋቂ ግለሰብ ጋር ሆቴል ተገኝተው እያወሩ ነው]

  • ሰላም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት ነህ?
  • አገሪቱ ወዴት እያመራች ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አገሪቱማ በለውጥ ጎዳና ላይ ናት፡፡
  • በነውጥ ጎዳና ማለትዎ ነው?
  • ምን ይላል ይኼ?
  • ክቡር ሚኒስትር ለምን የሚነገራችሁን አትሰሙም?
  • ምንድነው የተነገረን?
  • ሮድማፕ አዘጋጁ፡፡
  • የምን ሮድማፕ ነው?
  • ለውጡ ሮድማፕ ያስፈልገዋል፡፡
  • ሮድማፕ ምንድነው?
  • ለውጡ የሚጓዝበት አቅጣጫ ጠቋሚ ሮድማፕ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
  • ለምን ያስፈልጋል?
  • የምንሄድበትን እንድናውቀው ነዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የምንሄደውማ ወደ ልማት፣ ዲሞክራሲና ዕድገት ነው፡፡
  • እንዳይሸወዱ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እንዴት?
  • የተዘጋጀ ሮድማፕ ከሌለ በመሀል ጉዟችን ወደ ሌላ ሊሆን ይችላል፡፡
  • ወደ ሌላ ወዴት?
  • ወደ ዕልቂትና ፍጅት፡፡
  • አንተ ደግሞ ሁሌ ሕዝብ ማሸበር ትወዳለህ፡፡
  • እውነቴን ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ ያልኩት ለምን አልሆነም ማለት ትወዳለህ፡፡
  • እስከ ዛሬም እኔን ብትሰሙኝ እንዲህ ባልሆናችሁ ነበር፡፡
  • እንዴት? እንዴት?
  • ለውጡ እንዴት መሄድ እንዳለበት ነግሬያችሁ ነበር፡፡
  • አንተን ማን ነው መካሪ ያደረገህ?
  • ከእርስዎ ጋር እንዲህ መነጋገር አይገባንም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኮ ለምን?
  • በአሁኑ ወቅት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ስለአገሪቱ ዕጣ ፈንታ የመወሰን አቅም አለው፡፡
  • እሱስ ልክ ነው፡፡
  • እኔ ደግሞ ምን ያህል ተፅዕኖ ፈጣሪ እንደሆንኩ ያውቃሉ፡፡
  • ምን ይደረግ እያልክ ነው?
  • አሁንም የምንነግራችሁን ካልሰማችሁ አገሪቱ ወደባሰ ነገር መሄዷ አይቀርም፡፡
  • እንዴት?
  • ክቡር ሚኒስትር በየቦታው መፈናቀሉ እኮ በጣም እየጨመረ ነው፡፡
  • ምን ይደረግ?
  • ሁሉንም አካላት በጠረጴዛ ዙሪያ አስቀምጣችሁ አወያዩ፡፡
  • አሁን ከእኔ ጋርም መወያየት አለባችሁ ለማለት ነው?
  • መልሱን መቼም እርስዎም ያውቁታል፡፡
  • ወይ ጣጣ፡፡
  • የአገሪቱ ኢኮኖሚም ከድጡ ወደ ማጡ እያዘገመ ስለሆነ በአፋጣኝ ይታሰብበት፡፡
  • እ…
  • ለማንኛውም እኔ በግሌ ያሰብኩት ፕሮጀክት አለ፡፡
  • የምን ፕሮጀክት?
  • ለአገሪቱ በጣም ጠቃሚ ፕሮጀክት ነው፡፡
  • እሺ፡፡
  • ስለዚህ በአፋጣኝ እንዲሰጠኝ እፈልጋለሁ፡፡
  • ምን?
  • የውጭ ምንዛሪ፡፡
  • ስማ አገሪቱ ያላት የውጭ ምንዛሪ ለመድኃኒትና ለነዳጅ ነው ሲባል አልሰማህም?
  • ቢሆንም እኔ ለፕሮጀክቴ የውጭ ምንዛሪ እፈልጋለሁ፡፡
  • ምን ልትገዛ?
  • ላሰብኩት ፕሮጀክት ስልሳ አዝዣለሁ፡፡
  • ስልሳ ምን?
  • 8!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ ጋዜጠኛ ጋር ተገናኝተው እያወሩ ነው]

  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን ሆንክ?
  • ስንት ተስፋ አድርገንባችሁ፡፡
  • እኮ ምን ሆንክ?
  • ክቡር ሚኒስትር የእውነቴን ልንገርዎት፡፡
  • ንገረኝ፡፡
  • በለውጡ ትልቅ ተስፋ አድርጌ ነበር፡፡
  • አሁንም ተስፋ አትቁረጥ፡፡
  • አይ ክቡር ሚኒስትር በዚህ ከቀጠልንማ ትኬት መቁረጤ አይቀርም፡፡
  • የምን ትኬት?
  • አገር ለመክዳት ነዋ፡፡
  • ምን ሆንክ ደግሞ አንተ?
  • ዓይናችን እያየ እኮ አገሪቱ እንደ አውሮፕላናችን ልትከሰከስ ነው፡፡
  • የለውጡ አደናቃፊ ነህ ልበል?
  • ኧረ የለውጡ ደጋፊ ነበርኩ፡፡
  • ታዲያ አርፈህ ድጋፍህን ቀጥላ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እያስፈራችሁኝ ነው፡፡
  • ለውጥ እኮ ዝም ብሎ አይመጣም፡፡
  • ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው አሉ፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • ዝም ብላችሁ በቃላት እየሸነገላችሁን አገሪቱ ወዳልሆነ አቅጣጫ እያመራች ነው፡፡
  • ስማ ታፍኖ የነበረ ሕዝብ ነፃ ሲወጣ ከዚህም የባሰ ሊታይ ይችላል፡፡
  • ማን ነው ነፃ የወጣው?
  • ሁሉም ሕዝብ ነዋ፡፡
  • እ…
  • እናንተ ራሳችሁ እንደ ልባችሁ መናገር የጀመራችሁት አሁን አይደል እንዴ?
  • የመናገር መብታችን እኮ በአጭሩ ሊቀጭ ነው፡፡
  • ማን ነው የሚቀጨው?
  • እናንተው ናችኋ፡፡
  • እንዴት አድርገን?
  • ይኸው የጥላቻ ንግግር ሕግ እያወጣችሁ አይደል እንዴ?
  • የጥላቻ ንግግር ይፈቀድ እያልክ ነው?
  • እሱማ እንዲቆም እኔም እታገላለሁ፡፡
  • ታዲያ ምን እያልክ ነው?
  • ፈርዶብኝ በማር ውስጥ የተደበቀን መርዝ የመለየት ችሎታ አለኝ፡፡
  • አልገባኝም?
  • በዚህ ሕግ በኃላፊነት የሚሠሩ ሚዲያዎችም እንደሚታፈኑ አውቃለሁ፡፡
  • እ…
  • በፀረ ሽብር ሕጉ እኮ የተደረገው እንደዚያው ነው፡፡
  • እሱ እኮ ሊሻሻል ነው፡፡
  • ይሻሻላል ስትሉን እኮ በጥሩ መስሎን ነበር፡፡
  • በጥሩ ነው የሚሻሻለው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ያሻሻላችሁት ይኼኛው እኮ ይብሳል፡፡
  • እ…
  • ለማንኛውም የተባላችሁትን ልንገራችሁ፡፡
  • ምን ተባልን?
  • ትሻልን ፈተን…
  • እ…
  • ትብስን አገባን!

[ለክቡር ሚኒስትሩ አንድ ተመራማሪ ስልክ ይደውልላቸዋል]

  • በጣም አዝኛለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምን አዘንክ?
  • አገሪቱን እያሰብኩ ነዋ፡፡
  • ሁሉም ነገር መልክ መልኩን ይይዛል፡፡
  • ተው እንጂ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምነው?
  • ከዚህ በላይ አገሪቱ ምን እስክትሆን ነው የምትጠብቁት?
  • የተላለፈችልን አገር ምን ዓይነት እንደነበረች አትርሳ፡፡
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ላለፉት 27 ዓመታት ሕዝብ ከሕዝብ ጋር እንዲተላለቅ ሲሠራ ነበር እኮ፡፡
  • እሱንማ አውቃለሁ፡፡
  • ታዲያ የ27 ዓመት ወጣት እንዴት ከአንድ ዓመት ጨቅላ ጋር ይወዳደራል?
  • ሁሉም ነገር ይገባኛል፡፡
  • ስለዚህ የአገሪቱ ችግር እንዲህ በቀላሉ አይፈታም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር አሁን ችግሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየባሰበት እኮ ነው፡፡
  • የሴራ ፖለቲካውን እያወቅከው?
  • ቢሆንም በኋላ የታሪክ ተጠያቂዎች እንዳትሆኑ መጠንቀቅ አለባችሁ፡፡
  • ምን ማድረግ እንችላለን?
  • የአገሪቱ ኢኮኖሚ እኮ በአፍጢሙ እየተደፋ ነው፡፡
  • አገሪቱ እንዲህ እየታመሰች ኢኮኖሚው እንዴት ይረጋጋ?
  • በነገራችን ላይ ክቡር ሚኒስትር፣ ኢኮኖሚው መፍትሔ ቢያገኝ አገሪቱ ትረጋጋ ነበር፡፡
  • እንዴት?
  • ባለፈውም ነግሬዎት ነበር፡፡
  • ምንድነው የነገርከኝ?
  • ለወጣቱ የሥራ ዕድል ቢፈጠርለት በየቦታው ብጥብጥ ሊኖር አይችልም፡፡
  • እ…
  • ወጣቱ ወደ ጎዳና የሚወጣው የሚሠራው ስለሌለው ነው፡፡
  • እሱማ እናውቃለን፡፡
  • ስለዚህ ለወጣቱ ሥራ ፍጠሩለት፡፡
  • ሥራ ከተፈጠረለት ማን ይሠለፋል?
  • እ…
  • ማለቴ ለውጥ መኖሩ የሚታወቀው ሰው እንደ ልቡ መሠለፍ ሲችል ነው፡፡
  • አሁን ገባኝ፡፡
  • ምኑ?
  • እናንተ መፍጠር የምትፈልጉት ሥራ አይደለም፡፡
  • ታዲያ ምንድነው?
  • ሥራ አጥ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከደላላው ጋር እያወሩ ነው]

  • ሥራ እንዴት ነው?
  • ሁሉም ነገር ተቀዘቅዟል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አንተ ሁሌ መለኛ አይደለህ እዴ?
  • አዎን ግን አሁን ትንሽ ከበድ ብሏል፡፡
  • እና ሥራ የለም እያልክ ነው?
  • እሱማ አንድ ሐሳብ መጥቶልኝ ነበር፡፡
  • ምን ዓይነት ሐሳብ?
  • ያው ከለውጡ በኋላ የሥራ አጡ ቁጥር ጨምሯል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እሱማ ይታወቃል፡፡
  • በለውጡ ደግሞ ሕዝቡ እንደፈለገ ወደ ጎዳና ወጥቶ መሠለፍ ችሏል፡፡
  • ሥራ ከሌለ ቢሠለፍ ምን ያደርጋል?
  • አሁን ባሰብኩት ሐሳብ ለወጣቱም ሥራ ልንፈጥርለት እንችላለን፡፡
  • እንዴት?
  • በለውጡ ሁሉም ሰው መሠለፍ ይፈልጋል፡፡
  • እ…
  • ስለዚህ አጀንዳ ኖሯቸው ሠልፍ ለሚጠሩ ሠልፈኞችን ማቅረብ እንችላለን፡፡
  • እንዴት? እንዴት?
  • አዩ ክቡር ሚኒስትር እኛ ጎዳና የሚወጡ ሠልፈኞችን በማዘጋጀት አጀንዳ ኖሯቸው ሠልፍ ለሚጠሩ እናቀርባለን ማለት ነው፡፡
  • አንተ እኮ አባ መላ ነህ፡፡
  • ሠልፈኞችን ሲፈለግ በፆታ፣ ሲያስፈልግ በዕድሜ፣ ከዚያም በብሔርና በሃይማኖት እየከፋፈልን እናቀርባለን፡፡
  • ይኼማ ወሳኝ ሥራ ነው፡፡
  • ስለዚህ በአስቸኳይ ቢልቦርድ ላሠራ፡፡
  • ምን የሚል?
  • ሠልፈኞችን ከአሠላፊዎች ጋር እናገናኛለን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የመንግሥት ውዝግብ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት...

በኦሮሚያ ክልል በስድስት ከተሞች የተዋቀረውን ሸገር ከተማን የማደራጀት ሥራ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ስድስት ከተሞች የተዋቀረው ሸገር ከተማን...

በተቃርኖዎች መሀል የሚዋልለው የብልፅግና መንግሥት

ርዕዮተ ዓለም እንኳ የሌለው ይሉታል የሚቃወሙት ወገኖች፡፡ እሱ ግን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...

ዘምዘም ባንክ ለሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ

ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በማስተዋወቅ ቀዳሚ የሆነው...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...