Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉየኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄ ከየት ወዴት?

የኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄ ከየት ወዴት?

ቀን:

አንዳርጋው አሰግድ

ቅድመ ነገር

የ60’ዎቹ የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን የኢትዮጵያን የብሔሮች ጥያቄ በማንሳታቸው ይወቀሳሉ። አንዳንዶች የሚወቅሷቸው ‘ያልነበረንና የሌለን የብሔር ጥያቄ አንስተው. . .’ በማለት ነው። ለነዚህኞቹ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከጥንትም ተጋብተው፣ ተዋልደው፣ ተከባብረው፣ ተቻችለውና ተረዳድተው አብረው የኖሩ ናቸው። ሌላው ቀርቶ፣ የኢትዮጵያ ባለመሬቶችና ጭሰኞችም ተዛዝነውና ተሳስበው በሰላም የሚኖሩ ነበሩ። ሌሎቹ የሚወቅሷቸው ‘ባዕድ የሆነውን የማርክሲዝም ሌኒንዝም ስታሊኒዝም አመለካከትና አቋም በአገሪቱ ላይ ጭነው አገሪቱን የሚከፋፍልና የሚያፈራርስ ፖለቲካ አስፋፉ’ በማለት ነው። እነዚሆቹ ይህንን አመለካከታቸውን በየ አጋጣሚው ለመደጋገም እጅግ ትጉ ናቸው። የሚያስገርመው ግን እስከዚህም ትጋታቸው አይደለም። ለጥቂት ያዳመጣቸው የሚገመው ይልቁኑ፣ በእጅግ አብዛኞቹ ከማርክሲዝም ሆነ ከሌላ ሐፍት ስለጥያቄው አንድም ቅጠል ያላነበቡ ተቺዎች ሆነው በመገኘታቸው ነው። ወይም፣ ለይስሙላ ያህል ያነበነቡ ሆነው በመገኘታቸው ነው።

በሌላው ወገን ከ50’ዎቹ ጀምሮ የተነሱት የብሔር ድርጅቶች የየበኩላቸውን ሚና ተጫውተዋል። የነዚህኞቹ አመራሮች ተገቢ ጥያቄን ይዘው የተነሱና የታገሉ ቢሆኑም አባሎቻቸውንና ብሔራቸውን ለምሳ ዓመታት ሙሉ በበደሎች ትረካና በመገንጠል መብት ዙሪያ ብቻ ሲቀሰቅሱ፣ ሲያነሳሱና ሲያታግሉ ኖሩ። ታሪክን እንዳሻቸው እያፋሱ በመተረክ የስሜታዊ ተከታዮች ማበራከቻና የውጭ ድጋፍ መሸመቻ መሣሪያ ሲያደርጉት ኖሩ። ለሥልጣን ባለቤትነት ሲበቁ ደግሞ ሕዝቦችን በቋንቋ መሥፈርት አጥረውና ዛት ባለቤትነት ከልለው የመግዢያና የሥለጣን መጠበቂያ መሣሪያ አደጉት። ይባስና፣ የራሳቸውን ብሔር ጭምር የመበዝበዣና የመጨቆ መሣሪያ አድርገው ከበሩበት።

የኢትዮጵያ ሕዝቦች ተጋብተው፣ ተዋልደው፣ ተከባብረውና ተረዳድተው አብረው የኖሩ መሆናቸው ውነታ ነው። ከዚህ ውነታ ግን፣ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ጥያቄ አይነሳ የሚል መደምደሚያ ሊከተል አይችልም። ‘ባዕድ አመለካከት በአገሪቱ ላይ ጭነው’ የሚለውም መሠረት የለውም። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሕዝቦቿ ከሚከተሏቸው ስት ታላላቅ ሃይማኖቶች፣ ፍትሐ ነገሥትና ክብረ ነገሥት አንስቶ እስከ ወንጀለኛና የፍትሐ ብሔር ሕጎችና የተለያዩት ሕገ መንግሥቶች. . . ወዘተ. ድረስ “ከባዕድ” ያልመጣ ነገር የለም። ዛሪ በፊው የሚጠየቁት የሰብዓዊና የሞክራሲ መብት፣ የግልነት፣ የተጠያቂነት፣ የአካታችነት፣ የሕግ የበላይነት፣ የመልካም አስተዳደር. . . ጥያቄዎች ሁሉ አገር በቀል አይደሉም። ስለዚህም ይልቁኑ የሚበጀው፣ በነራዊ የነበረውንና ያለውን የብሔሮች መብት ጥያቄ በየምክንያቱ ከማድበስበስ ይልቅ በአንክሮ ለማየትና ለማስተዋል መድፈሩ ነው። አሁንም “ከባዕድ በመጡት” የሰጥቶ መቀበል የፖለቲካ ድርድር ዘዴዎች ለመፍታት በመሞከር ላይ ማተኮሩ ነው።

በዚህ ሑፍ ስለኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ አነሳስና ሒደት ታሪክ አጭር ማስታወሻ ለማቅረብ እሞክራለሁ። ይ ጥረቴ ከተመለከቱት ክፍሎች ጋራ ለመሟገት አይደለም። ከምሳ ዓመታት በኋላ ዛሬም በጥያቄው ላይ ለሚካሄዱት የተካረሩ ምልልሶች፣ በአንድ በኩል የታሪክ ጀርባውን ለማስታወስ ነው። በሌላውም በኩል፣ ጥያቄው ባለፉት ምሳ ዓመታት ውስጥ የሄደባቸው ምዕራፎች በመጠኑ እንኳን ቢታወቁ እንዳመጣ ከሚነገሩት ሐተታዎች ፈቀቅ ለማለት ይቻል ይሆናል። እንዲያም ሲል፣ ለሰከነ የፖለቲካ ውይይትና ድርድር የሚያግዝ አስተዋኦ ሊሆን ይችል ይሆናል የሚል ግምት ስላደረብኝ ነው።

የመጀመያዎቹ ዓመታት (1953 እስከ 1961)

የኢትዮጵያ ተራማጅ ተማሪዎችና ምሁራን የመሬት ላራሹንና የሞክራሲን ጥያቄ በ1957 ዓ.ም. ለመጀምያ ጊዜ አነሱ። ብዙም አልቆየ፣ የኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ በ1959 ዓ.ም. ታከለ። ጥያቄው መነሳት የጀመረው፣ እንደ መሬት ጥያቄ ነባራዊ አገራዊ ጥያቄ ስለነበር እንጂ አንዳንዶች እንደሚያትቱት ከአየር ውስጥ ተጨልፎና ለቲዎሪ ቅንጦት አልነበረም። ወይም፣ አንዳንዶች እንደሚሉት ‹‹የወቅቱ ተማሪዎችና ምሁራን በባዕዱ የማርክሲዝም ቀኖና ስለተለከፉ፤›› አልነበረም። ጥያቄዎችን እንዲያሱ ያደረጓቸው ሁኔታዎች ይልቁኑ፣ በአካባቢያቸው የሚያስተውሏቸው ነባራዊ ጉዳዮች ነበሩ።

ሲጀመር፣ ጠያቂው የተማሪ ክፍል እንዳመጣ ይጣሉ የነበሩትን ወቅቱን አስነዋሪ፣ ጋንጢጥና አቃቃሪ አባባሎች የሚቃምና የሚያወግዝ ነበር። ‹‹ከአነጋገር ይፈረዳል ከአያያዝ ይቀደዳል›› የሚለውን የአባቶች ብሂል እያስታወሰ፣ የዜጎቿ ማንነትና ሰዓዊ ክብር እንዲታወቁና እንዲከበሩ የሚያስተምርና የሚቀሰቅስ ነበር። ወይም፣ ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ገና በ20’ኛው ክፍለ ዘመን መጀመያ ላይ “መንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር” በተባለው መሐፋቸው፣ ‹‹መንግሥት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም። አስተካክለን ካሰብን ዘንድ፣ መንግሥት መቆሙ ለሕዝቡ ነው። ጥረቱ ሕዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግሥት ሊቆም አይችልም። ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ማድላት ለመንግሥት የሚገባው ሥራው አይደለም፤›› ያሉትን ቁም ነገር የራሱ ያደረገ ነበር።

 

ነገር ግን በዚያው በተማሪና ምሁር አካባቢ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሁኔታም ነገሮች ጠለቅ ተበሎ እንዲታዩ የሚገፋ ነበር። አንደኛው ጉዳይ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ በሚሰጠው ፈተና ለአማርኛ ቋንቋ ዕውቀትና ችሎታ ከፍተኛ ሥፍራ ይሰጥ ነበር። ይህ አሠራር የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ያልነበሩትን ተማሪዎች የሚያበሳጭ ብቻ አልነበረም። የከፍተኛ ትምህርትና የሥራ ማግኘት ዕድላቸውንም የሚወስን ጉዳይ ነበር። ስለነበረም፣ ተራማጅ ተማሪዎችና ምሁራን ያልተቀበሉትና ፍትሐዊነቱን እንዲጠይቁ ያስገደደ ጉዳይ ነበር።

በዚህ ላይ ደግሞ፣ በተፈጥሮው ከተለያዩ ብሔሮች የሚመጡትን ተማሪዎችና ምሁራን ባቀፈው የዩኒቨርቲ ማኅበረሰብ ውስጥ የብሔሮች ጥያቄ በተለያዩ አጋጣሚዎች እየተነሳ አንዳንዴም በአካል እስከ መጋጨት ያደርስ ነበር። ደግሞም፣ ከዛው ከዩኒቨርሲቲው ሳይርቅ ዓመቱን እየጠበቀና ጥምቀትን እየቆጠረ በጃንሆይ ሜዳ በሚካሄደው በዓል ላይ በተለያዩ የብሔሮች የዘፈን ቡድኖች መካከል ግጭቶች ይነሱ ነበር። ራቅም ሲል፣ የካምቦሎጆ የቡድኖች ቲፎዞዎች ግጭቶች ነበሩ። እነዚህን ሁነቶች በቅርብ ይከታተሉ የነበሩ ተማሪዎችና ምሁራን ግለሰባዊና ቡድናዊ የሚመስሉት ግጭቶች ወት ሊያመሩ እንደሚችሉ ይጠይቁና ይወያዩ ነበር። በሌላውም ወገን፣ የዩኒርሲቲ ተማሪዎች ለሔራዊ አገልግሎት በየ ገጠሩ ይሠማሩ ነበር። ከየ ሄዱበት ይዘውት የሚመለሱት መረጃና ግንዛቤ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ሥርዓትና አመራር ላይ ዙ ጥያቄዎችን የሚቀሰቅስ ነበር።

ከዚህም በላይ ግን፣ በ1953 ዓ.ም. የመጀመያው ጥይት በኤርትራ ምድር ተተኮሰ። በ1955 ዓ.ም. የሜጫ ቱለማ ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ተመሠረተ። በዚሁ ዓመተ ምረት በሶማሊያ መንግሥት የተደገፈው የባሌ ገበሬዎች እንቅስቃሴ ተነሳ። ከላይ በተመለከቱት ሁኔታዎች ላይ የነዚህ እንቅስቃሴዎች መታከል፣ ተራማጅ ተማሪዎችንና ምሁራንን ንግዲህ ምክያቶቹን አጥብቀው እንዲጠይቁ አደረጓቸው። ፖለቲካዊ መልሶችን የመሻት ጉዞ ተጀመረ። የመጀመያው ግል ውይይት የተደረገው በ1959 ዓ.ም. ነበር። ብሔራዊ የኢትዮጵያ ዩኒቨር ተማሪዎች ማኅበር ስድስተኛ ጉባዔ በመጋቢት 1959 ዓ.ም. ተደረገ። ‹‹በኢትዮጵያ ስለሚገኙ ከፋፋይ ንቅናቄዎች›› በሚል ርዕስ ተካሂዶ ስለኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ የመጀመያውን የተማሪ ማኅበር ውሳኔ አሳለፈ። ሁለተኛው፣ በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር በነሐሴ 1960 ዓ.ም. በዩጎዝላቪያዛግሬብ ባደረገው ስምንተኛ ጉባዔ ላይ የተወሰነው ነበር። ስተኛው፣ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር በነሐሴ 1961 ዓ.ም. በተካሄደው 17’ኛ ጉባዔ ላይ የተወሰነው ነበር።

በሌላው በኩል፣ ከ50’ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ በተለያዩት የተማሪ ማኅበራት መሔቶች ላይ (ታገል፣ ታጠቅ፣ ትግላችን፣ ቻሌንጅ) ስለብሔሮች ጥያቄ የተያዩ ሑፎች ይወጡ ነበር። ከመጀመያዎቹ አንደኛው፣ “ኢትዮጵያዊው ማነው?” በማለት የጠየቀው የኢብሳ ጉተማ ግጥም ነበር። ከያም፣ ኃይሌ ፊዳ በሚያዝያ 1960 ዓ.ም. ‹‹የኤርትራ ሕዝብ ትግል ተገቢ አጀማመር ሕዝባዊ ያልሆነ አመራር፤›› በሚል ርዕስ ‘‘ወርዶፋ ገመዳ’’ በሚ የብዕር ስም ለታጠቅ መሔት ያቀረበው ሑፍና የሰሜን አሜሪካ ተማሪዎች ማኅበር መሪዎች ቻሌንጅ ይባል በነበረው መሔት ላይ በ1961 ዓ.ም. ያቀረቧቸው ጥናታዊ ሑፎች ተከተሉ። ዋለልኝ መኮንን “On the question of Nationalities in Ethiopia” በሚል ርዕስ ያቀረበው ሑፍ በኅዳር 1962 ዓ.ም. ወጣ።. . . ይህ በዚህ እንዳለ፣ ዘመኑ በሌላው በኩል ደግሞ እንደነ ዮሐንስ ስብሃቱ ያሉት የተማሪው ማኅበር ንቁ ተሳታፊዎች የኤርትራን የነፃነት ግንባሮችን ለመቀላቀል ወደ በር ያቀኑበት ዘመን ነበር።

በዘመኑ በግልና በፊው ይካሄዱ በነበሩት ውይይቶች፣ በየ ጉባዔዎቹ ውሳኔዎችና በተከታታይ ይወጡ በነበሩት ሑፎች ላይ የ ዮሐንስ ርምጃ መከሰት ግርታን ያሰፈነ ሁነት ብቻ አልነበረም። አንዳንድ የተማሪ ማኅበራት መሪዎች የነ ዮሐንስን ርምጃ በወቅቱ በትክክል እንዳነበቡት የመውን ዘመን አጣጫ ያመለከተ ሁነትና ስለኢትዮጵያ ወደ ፊት ዙ ጥያቄዎችን የጫረ ነበር። ስለነበርም፣ የወቅቱ ተራማጅ ተማሪዎችና ምሁራን ለብሔሮች ጥያቄ ተገቢውን ትኩረት ሰጥተው ለመንቀሳቀስ ወሰኑ። የተጠቀሱትን የተማሪ ማኅበራት ጉባዔዎች ውሳኔዎች ዛሬ ተመልሶ የሚያነብ፣ ትግሉ ከየት እንደ ጀመ በቀላሉ ሊገነዘብ ይችላል። ብሔራዊ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማበር ስድስተጉባዔ ውሳኔ ለምሳሌ፣ የሚከተለው ነበር።

  • በኢትዮጵያ ውስጥ ከፋፋይ ንቅናቄዎችን ለማነሳት በተደጋጋሚ ሙከራዎች እየተደረጉ መሆናቸውን በመገንዘብ፣
  • የመሀከለኛው ምሥራቅ አድኃሪ የዓረብ ኃይሎች በዚህ ቅስቀሳ ላይ ያላቸውን ፅኑ ፍላጎት በመገንዘብ፣
  • በእንደዚህ ዓይነት ከፋፋይ ንቅናቄዎች ላይ ንዑስ ከበርቴዎች፣ አድባርዮችና አድኃሪዎች ያላቸውን ልዩ ጥቅም በመገንዘብ፣
  • ይህንንም ፀረ አንድነትና አድኃሪ ኃይሎች ለማራገብ ያላቸውን ፍላጎት በመገንዘብ፣
  • እንደዚህ ዓይነት ቡርዣዊና አድኃሪ የሆነ አመለካከት መስፋፋት የብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ምሥረታን የሚያሰናክል መሆኑን በመገንዘብ፣
  • እነዚህ አዝማሚያዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ቀኛ የፖለቲካ ትምህርት ሒደት እንደ ሚያፋልሱና እንደ ሚመርዙ በመገንዘብ፣
  • እንደዚህ ዓይነቱ ከፋፋይነት ኢምፔሪያሊስቶች ለራሳቸው መጠቀሚያ ሊያደርጉት እንደሚችሉ በመገንዘብ፣ ፊውን ሕዝብ በተደጋጋሚ በማወናበድ ላይ ካሉ ከሃዲዎንና አድርባዮች ራሱን በንቃት እንዲጠብቅ ለሞክራሲያዊ ኃይሎች ሁሉ ጥሪ ያቀርባል። የነሐሴ 1960 ዓ.ም. የአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ስምንተኛ ጉባዔ ውሳኔም የሚከተለው ነበር
  • ‹‹ሕዝባዊ መንግሥት ቋንቋንና ነገድን የሚከፋፍለውን ሁሉ አጠቃሎ ሲሰርዘው ሕዝቡ በቀላል የሚማርበትን ቋንቋንና ነገድን የሚኘውን ቋንቋ ከባህሉ ጋር ደግፎ እንዲስፋፋ የማበረታቻ ዘዴ ይፈልጋል፣
  • የኤርትራ ግንባ አመራር የሚከተለው ፖለቲካ የኤርትራን ሠራተኛና የገበሬ ጥቅምና ፍላጎት የማያረካ፣ የታጋዩን ሕዝብ ድል ለመሻማት የታቀደ ፖለቲካ መሆኑን በመገንዘብ በጥብቅ ይኮንነዋል። የኤርትራን ሕዝብ ትክክለኛ ተጋድሎ ይደግፋል፣
  • የዚህ ማኅበር ምኞት በእኩልነትና በነፃነት ላይ የተመሠረተች፣ በነገድ፣ በዘር፣ በቋንቋና በሃይማኖት ያልተከፋፈለች አዲስ ሕዝባዊት ኢትዮጵያ እንድትመሠረት ነው››።

መኢሶን በሐምሌ 1960 ዓ.ም. ተመሠረተ። በመመሥረቻው ጉባዔ ላይ የብሔሮችን ጥያቄ በሚመለከት የተነሳው ውይይት በቅድሚያ በቅራኔዎች አቀማመጥ ጥያቄና በመርሆዋዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። ‘ከሁሉም በላይ ተፃራሪ የሆነው ወይም ሊታረቅ የማይችለው መሠረታዊ ቅራኔ በመደቦች መከል ያለው ቅራኔ ነው። በብሔሮች መከል ያለው ቅራኔ በሁለተኛ ደረጃ መታየት ያለበት፣ መሠረታዊው ሲፈታ ተያይዞ የሚፈታና እንዲያም ሲል በሞክራሲያዊ መንገድ ሊታረቅ የሚችል ነው’ ከሚለው አጠቃላይ ስምምነት ላይ ተደረሰ። እንደዚሁም ‘የብሔሮች መብት በመርሆ ደረጃ የሚታወቀው በተለያዩ የአስተዳር መንገዶች አብሮ ከመኖር አንስቶ እስከ መገንጠል ድረስና መገንጠልንም ጨምሮ እንደሆነ’ ተቀበለ። ከዚህ የመርሆ አቋም ባሻገር ለመገንጠል ጥያቄ ድጋፍ የሚሰጥበትንየማይሰጥበትን ሁኔታዎች በጭብጥና በሳባዊ ደረጃዎች መመልከት በተጀመረበት ጊዜ ክርክሩ ሞቀ። በተለይ የኤርትራን ጥያቄ በተንተራሰ ስለመገንጠልና ስለኤርትራ ግንባር አመራር ተፈጥሮ (በዚያን ጊዜ የነበረው በኦስማን ሳላህ ሳቤ የሚመራው ግንባር ነበር) ከፍተኛ ክርክር ተነ። ክርክሩ ግንባሩ ተራማጅ ነው ወይስ አይደለም? በግንባሩ ሥር ነፃ የወጣች ኤርትራ ከብዝበዛና ከጭቆና ነፃ የወጡ ኤርትራውያ ምድር ትሆናለች ወይ? ትግሉ እየገፋ ሲሄድ ምን መልክ ይይዛል?. . . ወዘተ. በሚሉት ጥያቄዎች ዙሪያ የተካሄደ ነበር። በመጨረሻም ‹‹የሕዝቡ ተጋድሎ መደገፍ አለበት ይሁንና ፀረ ሞክራሲና ጎሰኛ የሆነውን የግንባሩን አመራር በግል መቃወምና ማውገዝ ያስፈልጋል፤›› ከሚለው አጠቃላይ ስምምነት ላይ ተደረሰ። ይህም ይብዛም ይነስም፣ ኃይሌ ፊዳ በሚያዝያ 1960 ዓ.ም. ለታጠቅ ሔት አቅርቦት ከነበረው ሑፍ ጋር አንድ ዓይነት አመለካከት ነበር። መኢሶን ሁል ጊዜም ያራመደው አቋም ነበር።

ነገር ግን ‹‹በዚህስ ሁኔታ? በዚያስ ሁኔታ?. . . በሚሉ ነጥቦች ዙሪያ ብዙ ጥያቄዎች ተነሱ። አንዳንዶቹ ተገንጣዩ ተራማጅና ወደ ሶሻሊዝም የሚጓዝ ከሆነ የሚለውን ቅድመ ሁኔታ ሲያስቀምጡ ሌሎች ወደ ሶሻሊዝም የማይሄድም ቢሆን መደገፍ አለበት የሚለውን አቋም ያዙ። የተደረገው ረጅም ውይይት የተነሱትን በርካታ ጥያቄዎች የፈታ አልነበረም። በመጨረሻ በፕሮግራሙ የፈረው የሚከተለው አንቀም ጉባው የደረሰበትን ውሳኔ የሚያንባርቅ አልነበረም

  • ‹‹በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ነገዶች መከል የሚታየውን የሁለተኛ ደረጃ ቅራኔ በማጥፋት ከየ ነገዱ ከል መልካሙ ቅርስ እየተወሰደ ስምምነት፣ የአገር ፍቅርና ፊ አስተያየትን የሚያዳብር አዲስ ዓይነት ሕዝባዊ ባህል እንዲለማ ይደረጋል።
  • ‹‹በነገዶችና በጎሳዎች መከል ኩልነትን መፍጠር። በአዲስ መሠረት ላይ አንድነታቸውን መገንባትባህላቸውንና ቋንቋቸውን መጠበቅና ማክበር›› ከአንቀ እንደሚታየው ብሔሮች የራሳቸውን ድል በራሳቸው ለመወሰን ያላቸው መብት ‹‹እስከ መገንጠልና መገንጠልንም ጨምሮ ድረስ መሆኑን›› ያሳወቀ አልነበረም። በዚህ መልክ የተፈውም፣ ፕሮግራሙ በመንግሥት እጅ የወደቀ እንደሆነ በንቅናቄው ላይ ‹‹አገር ከፋፋይ፣ ገንጣይና. . . ወዘተ.›› የሚለውን ዘመቻ ለመክፈት እንዳያመች አስቀድሞ ለመከላከል በማሰብ ስለወሰነ ነበር። በዚያ ወቅት ለእንደዚህ ዓይነቱ ዘመቻ ተመቻችቶ መቅረብ እንኳን ከሕዝብ ቀርቶ ከራሱ ከተማሪው ብረሰብ የሚነጥል ነበር። ከላይ የተታወሱት የማኅበራቱ ውሳኔዎች የሥጋቱን ነራዊ ምክንያት በበቂ ያመለክታሉ።

ለማንኛውም፣ የተጠቀሱትን የተማሪ ማኅበራት ውሳኔዎችንም ሆነ የነዋለልኝ ዓይነቱን ሑፍ ያልተቀበሉ ተማሪዎችም ነበሩ። ያልተቀበሏቸው፣ በአንድ ወገን ውሳኔዎቹን ከሞክራሲያዊና ከሰብዓዊ መብቶች ዕውቅናና ከፖለቲካዊ መፍትሔ መንገዶች አንፃር ሩቅ ሆነው ስላገኟቸው ነበር። በሌላውም ወገን፣ የ ዋለልኝ ዓይነቱን አቀራረብና አካሄድ እጅግ ጥራዝ ነጠቅና የአጉል መንገድ ቀስቃሽ ሆኖ ስላገኙት ነበር። በዚሁም ለማለት ይቻላል ሁለተኛው ምዕራፍ ተከፈተ።

ሁለተኛው የውይይትና የውሳኔዎች ምዕራፍ (1962 እስከ 1963)

አንዳንዶችና በተለይም ሕወሓትና ኦነግ የዋለልኝን ሑፍ እንፈር ቀዳጅ እያውለበቡ ብዙ ብዙ ሲሉ ይሰማሉ። አቶ ሌንጮ ለታ በአንድ በአሜሪካ በተደረገ ስብሰባ ላይም ‹‹እናንተ (ታዳሚዎቹን ማለታው ይመስለኛል) ዋለልኝን ካልፈለጋችሁት እኛ እንወስደዋለን፤›› እስከማለት ሄደው ነበር። ይሁንና፣ የዋለልኝ ሑፍ በኢትዮጵያ ተራማጅ ተማሪዎችና ምሁራን ዝክር ውስጥ ለአፍታ ብቅ ብሎ የጠፋ በራሪ እንጂ ሕወሓትና ኦነግ አጋነው እንደሚያራግቡት ይህ ነው የሚባል ሥፍራ የነበረው አልነበረም።

ከላይ እንደተመለከተው የውጭው የተማሪ ማኅብራት መሪዎች በወቅቱ የተመለከቱት እንደውምእጅግ ጥራዝ ነጠቅና ግጭት ጠሪ አድርገው ነበር። ዋለልኝ መኮንን ገና በሑፉ መግቢያ ራሱ እንዳለው፣ ሑፉ ‹‹ከአጠቃላይ ገለ የማያልፍና ተገቢውን ትንተና ያላደረገ ጉስቁል ያለ ጽሑፍ፤›› ነበር (The Article. . . Suffers From Generalizations and Inadequate Analysis)። ዋለልኝ በሑፉ ብሔሮች የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው ለመወሰን እስከ መገንጠል ድረስ ያላቸው መብት እንዲታወቅ የሞገተ ቢሆንም የብሔር እንቅስቃሴዎችን የሚደግፈው መብቱ እንደ መብት እንዲታወቅና እንዲከበር አልነበረም። ይልቁኑ፣ የብሔሮች ትግል ለሶሻሊዝም ለሚደገው ትግል ማራመጃና ማሳኪያ መሣሪያ ለመሆን ይጠቅማል ከሚል የትግል መሣሪያነቱ ሳብ አንፃር ነበር። በሌላ አገላለ፣ ዋለልኝ የኢትዮጵያን ሔሮች ጥያቄ የተመለከተው ከሽጉጥና ከክላሽን የማይለይ የትግል መሣሪያ አድርጎ ነበር።

ዋለለኝ ስለዚህም በአንድ በኩል ለመገንጠል የሚታገሉት የኤርትራ ግንባሮች የሶሻሊስት ግብ እስካላቸው ድረስ ወታደራዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸው የጠራ ነበር። በሌላው በኩል፣ የብሔር እንቅስቃሴዎች አገዛዙን የሚያዳክሙ ስለሆኑ፣ መደገፍ አለባቸው የሚለውን አስተሳሰብ ያራመደ ነበር። እዚህም ላይ በአንዳንድ የብሔር ድርጅቶች አመራሮች ዘንድ የብሔሮችን መብት ጥያቄ የብሔር ወገንን የመቀስቀሻ፣ የማደራጃ፣ የማታገያና የሥልጣን መጨበጫ መሣሪያ አድርጎ የመጠቀም ዘዴና አካሄድ የተነሰው ምናልባት በዚህ ጊዜ ይሆናል ቢባል ሊያስኬድ ይችላል። ሕወሓትና ኦነግ ዋለልኝን አብዝተው የሚያሞካሹትም በዚሁ ምክንያት ይሆናል። ለሥልጣን ሲበቁ ከላይ እንደተመለከተው፣ የመግዢያና የሥልጣን መጠበቂያ መሣሪያ አደረጉት።

ያም ሆነ ይህ፣ በ1962 ዓ.ም. ዋለልኝ ቡድን በተማሪው ጋዜጦች ላይ ይወጡ የነበሩት ጽሑፎች ከተማሪ ንቅናቄ ሥፍራና ሚና አልፈው በመሄድ ተማሪውን ለትጥቅ ትግል ጠሪና ቀስቃሽ ነበሩ። እንዲያውም ‹‹አብዮታዊው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ የአገሪቱን የአብዮት ኃይሎች እንቅስቃሴ ለመምራት ከሚችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፤›› እስከ ማለት የሄዱ ነበሩ። ስለነበሩም፣ የንጉሠ ነገሥቱንም መንግሥት ትኩረት የሳቡ ነበሩ።

ከወቅቱ የመንግሥት ጋዜጦች አዲስ ዘመን ለምሳሌ ‹‹ሕግን ለመጣስ፣ በሕይወትና በንብረት ላይ ጥፋት ለማድረስ የሚደረገውን ሙከራ ለመከላከል፤›› እያለ ‹‹መንግሥት ያለበትን ኃላፊነትና የሚወስደውንም ርምጃ ተማሪዎችም ሆኑ ወላጆቻቸው አስቀድመው ሊገነዘቡት ይገባል፤›› የሚል ነበር (ኅዳር 19)፡፡ የዛሬይቱ ኢትዮጵያም፣ ‹‹የኢትዮጵያን ጥቅምና ዕድገት የሚቃወምን ጨርሶ ለማስወገድ ካልተቻለ ሰላምና ፀጥታ ዋስትና አይኖረውም፤›› እያለ የሚያትት ነበር (ኅዳር 20)። የኢትዮጵያ ድምፅም፣ ‹‹ሺሕ ዓመታት የቆየውን ሥርዓት ተማሪዎች ሊያናውጡ ከፈለጉ ሕጉ ይበቀላቸዋል፤›› በሎ አትቶ ነበር (ኅዳር 20)። ኢትዮጵያ ሄራልድ በበኩሉ፣ ‹‹ባለ ሥልጣኖች ከእንግዲህ ምረት እያደረጉ መቀጠል አይገባቸውም። የተማሪዎች መሔት ባለፈው ሳምንት መታገዱ ትክክለኛው አቅጣጫ እንደተያዘ ይመሰክራል። ይህንን አቅጣጫ እስከ መጨረሻው ድረስ መከተል የማይታለፍ ነው፤›› እያለ፣ መንግሥት ጠንካራ ርምጃ እንዲወስድ የሚጠራ ነበር (ታኅስ 4)።

ታገል የሚባለው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሔት ኅዳር 5፣ ቀን 1962 ዓ.ም. ታገደ። ታኅሳስ 19 ቀን 1962 ዓ.ም. ጥላሁን ግዛው ተገደል። ተማሪው በፍላት ወጣ። ታኅሳስ 20 እና 21 ዕለት በደረሰው ግጭት በወቅቱ እንደተባለው ከ50 የማያንሱ ተማሪዎች ይወት በዩኒርሲቲው፣ በመድኃኔ ዓለም፣ በአርበኞች፣ በሐረር መድኃኔ ዓለም ትምህርት ቤቶችና በሃረማያ ኮሌጅ አለፈ። ከዚህ በኋላ በርካታ ተማሪዎች ወደ ውጭ አገሩ ወጡ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮና የዚህም ውጤት ሆኖ ለማለት ይቻላል በኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ ላይ የሚደረገው ውይይት በውጭ አገሮች ሆነ። ወደ ውጭ ከወጡት ተማሪዎች መካከል አንደኛው እንደሚታወው፣ በነሐሴ 1961 ዓ.ም. አውሮፕላን ጠልፎ ወደ ሱዳን የወጣውና በኋላም ወደ አልጄሪያ የተዛወረው የብርሃነ መስቀል ረዳ ቡድን ነበር። በ1962 ዓ.ም. ብዙዎም ወደ ሱዳን፣ ባኖን፣ ሞስኮና አሜሪካ ወጡ።

እኔ እስከ ማስታውሰው ድረስ፣ የዋለልኝ ሑፍ በውጭው ማኅበራት ዘንድ ግርምትና በአሳሳቢ ከመታየቱ በስተቀር የመወያያ ርዕስ ሆኖም አያውቅም። ሥፍራ የነበራቸው ይልቁኑ፣ የሰሜን አሜሪካው ማኅበር መሪዎች በ1961 ዓ.ም. ያወጧቸው ሑፎች፣ የዚሁ ማኅበር 17’ኛ ጉባዔ ውሳኔና ጥላሁን ታከለ በሚል የብዕር ስም በመስከረም 1963 ዓ.ም. የተሠራጨው የብርሃነ መስቀል ረዳና የኢያሱ ዓለማየሁ ሑፍ ነበሩ። የአሜሪካው ማኅበር መሪዎች ሑፍና ውሳኔ ታሪክ ጠቀስና ይበልጥም ትንተናዊ የነበሩ ቢሆኑም የኢትዮጵያን የብሔሮች ጥያቄ ያጤነው ከቀናዊ ቅራኔና ግጭት አንፃር ስለነበር በሌሎቹ ተራማጅ ተማሪዎችና ምሁራን ዘንድ ተቀባይነት አልነበረውም። የነብርሃነ መስቀል ሑፍ በበኩሉ በእንካ ሰላንትያ፣ በቅሎች፣ በስያሜዎችና በስድብ ጋጋታዎች የተሞላና የታወቁትን የማርክሲስት ወይም ሌኒኒስት ቲዎሪዎች በረጃጅሙ እየጠቀሰ ከመደርደር ያላለፈ ነበር።

የመኢሶን ጽሕፈት ቤት የሁለቱንም ክፍሎች አያያና አካሄድ ከገመገ በኋላ፣ በአውሮፓ ተማሪዎች ማኅበር አማካይነት ተማሪዎች በያሉበት ሥፍራ ሁሉ በየጥናት ክበቦቻቸው ስለብሔሮች ጥያቄ ቲዎያዊና ተሞክዊ ጥናቶችን በአራት አርዕስት ላይ አተኩረው እንዲያደርጉ ገፋ። የተመረጡት አርዕስት የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ መንግሥት አመሠራረትና ደት፣ ማርክሲያዊ ትተናና ማርክሲዝም ለብሔሮች ጥያቄ የሚያቀርበው መፍት፣ ከአፍሪና ከእስያ ቅኝ ተገዢ አገሮች የነፃነት ትግሎች የሚገኘው ተመክሮና ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ውሳኔዎችና ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ነበሩ። ሌላው ግፊት፣ የአውሮፓ ተማሪዎች ማኅበር ተከራካሪዎቹ ወገኖች ሁሉ የሚሳተፉበትንና በግል የሚወያዩበትን ጉባዔ እንዲያዘጋጅ የማድረግ ነበር።

በዚሁም ለማለት ይቻላል 1963 ዓ.ም. በአንድ ወገን የኢትዮጵያ ተማሪዎችና ምሁራን በየ ጥናት ክበቦቻቸው ስለብሔሮች ጥያቄ በፊውና በዝርዝር ያጠኑበትና የተወያዩበት ዓመት ሆነ። ጥናቶቹ የሚካሄዱት በከተማው በሳምንት አንድ ቀን ይደረጉ በነበሩት የጥናት ክበቦች ስብሰባዎች ላይ ነበር። ዓመቱ በሌላውም ወገን፣ ለተባለው ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት ዓመት ነበር። የአውሮፓ ተማሪዎች ማኅበር 11’ኛ ጉባዔ በነሐሴ 1963 ዓ.ም. በበርሊን ከተማ ሲደረግ በኢትዮጵያ ተማሪዎች ታሪክ ውስጥ በየ ማኅበሮቹ ውስጥ ያሉትን ኃይሎች ሁሉ አንቀሳቅሶ የተደረ ጉባዔ ሆነ።

ከአውሮፓው ማኅበር የማበሩን 11 ቅርንጫፍ ማኅበሮች የወከሉ 150 አባሎች ተሳፉ። ከሰሜን አሜሪካ አምስት የማበሩ አባሎችና በተለይም በዚያ የነበሩትን ሁለት መስመሮች ይወክሉ የነበሩት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴና ናይ ልኬ በአንድ በኩልና የ“ስፓርክ” አዘጋጅ የነበረው መስፍን ሀብቱ በሌላ በኩል ተገኝተው ነበር። የ“ጥላሁን ታከለ” ሑፍ አዘጋጆች የነበሩት ብርሃነ መስቀል ረዳና ኢያሱ ለማየሁ ከአልጄሪያው ቡድን ተገኝተው ነበር። ተስፋዬ ታደሰም ከሌባኖን። ከመስኮብም፣ በክፍሉ ታደሰ ዙሪያ የነበረው “የፋና” ቡድን ተገኝቶ ነበር። ከሆላንድም በመላኩ ተገኝ ዙሪያ የነበረውና በኋላ “ቡሌቲን” የተባለን ጋዜጣ ያወጣ የነበረው ቡደን ተሳትፎ ነበር። አላለፋቸውን በሚመለከተው፣ የአሜሪካው 17’ኛ ጉባዔ ውሳኔ ባለቤቶችና ደጋፊዎች የነበሩት እነ ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴና ናይ ልኬ በአንድ ወገን ሲሆኑ ሌሎቹ የነሱን አመለካከትና አቋም በመቃወም የተለፉ ነበሩ። ጉባዔው ሲፈም፣ የሚከተለው ውሳኔ በአብዛኛው ተሳታፊ ድምፅ ተደግፎ ደቀ። ማኅበሩ“አንደኛ፣ ብሔሮች የገዛ ዕድላቸውን ለመወሰን ያላቸውን በምንም ዓይነት የማይደፈር መብት ያውቃል። ይህም መብት መገንጠልንም ጭምር የሚጠቀልል ሲሆን እንዲታወቅ ከመታገል አያቋርጥም

“ሁለተኛ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ የሚገኙ ብሔሮች ተበዝባዦች በሙሉ የጋራ ጠላቶቻቸውን ለመደምሰስ ፀረ ፊውዳልና ፀረ ኢምፔሪያሊት የሆነ የትግል አንድነት እንደሚያስፈልጋቸው ያምናል። ለዚህ የትግል አንድነት ማኅበራችን ውስጥ የሚገኙ ከየ ብሔሩ የተውጣጡ ተራማጆች በሙሉ የማያቋርጥና የተቀነባበረ የማስተማር ትግል ማድረግ አለባቸው፣ ‹‹ነገር ግን ይህ አንድነት ሊገኝ የሚችለው እነዚህ ብሔሮች በአንድነት ለመኖር ፈቃደኛ ነው ሲገኙ ብቻ ነው። በዚህም መልክ በአንድ ሕዝባዊ መንግሥት ር ለመኖር የተፈቃቀዱ ብሔሮች ሙሉ በሙሉ እኩልነታቸው እንዲታወቅና የገዛ ኑሮአቸውን በያሉበት በመሰላቸው ለማስተዳደር ያላቸው መብት በማያወላውል ሁኔታ መረጋገጥ አለበት››

የአሜሪካው ማኅበር በዚሁ በነሐሴ 1963 ዓ.ም. ባካሄደው 19’ኛ ጉባዔው ላይ ይህንኑ ውሳኔ በተመሳሳይ አደቀ። ደርግ ወደ ሥለጣን እስካቀናበት 1966 ዓ.ም. ድረስ የአብዛኛው የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን አመለካከትና አቋም ከይ የተጠቀሰው ነበር። ይሁንና፣ በ1967 ዓ.ም. የተመሠረቱት ሕወሓት በበኩሉ ‹‹የኢትዮጵያ ዓይ ቅራኔ በብሔሮቿ መካከል ያለው ቅራኔ ነው፤›› በማለት ወጣ። ኦነግም፣ “የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው” እለ “ቅኝ ግዥዋን ኢትዮጵያ ለመዋጋት” ተነሳ። እዚህም ላይ፣ በብሔሮች ጥያቄ አንፃር የዛይቱን ኢትዮጵያ ሁኔታዎች ያበጀውና ያፈነው መሠረታዊ ይዘት ደርግ፣ ሕወሓትና ኦነግ ከ1967 ዓ.ም. ጀምሮ የሄዱት መንገድና የኤርትራ ግንባሮች ከድሮውም የሄደበት መንገድ ነበር ቢባል ውነታ ነው።

የአብዮቱ ዘመን ውይይቶችና አመለካቶች (1966 እስከ 1969)

የኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄ በ1966’ቱ የሕዝባዊ ንቅናቄ ዘመን ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል አንደኛው ነበር። በአብዮቱ ከተሳተፉት ድርጀቶች መካከል መኢሶንና ኢጭአት የ1963’ቱን ውሳኔ በማራመድ ለብሔሮች መብት መታወቅና መከበር በመታገል እንደኑ ቆይተዋል። ኢሕአፓም አልፎ አልፎ ከታዩት የአንዳንድ የአመራሩ አባላት መዛነፎች በስተቀር በ1963 ዓ.ም. መንፈስ ቆይቷል። ደርግ በሌላው በኩል ግን፣ ከ1966 እስከ 1969 እና ከ1969 እስከ 70 በኋላ በኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ ረገድ ለ17 ዓመታት የሄደበት መንገድ ሁሌም አንድና ያው አልነበረም። አካሄዱን በሦስት ወቅቶች ከፍሎ ማጤኑ ደቱን ግል ሊያደርግ ይችላል።

የመጀመያው ከሰኔ እስከ ሐምሌ 1966 ዓ.ም. እስከ ኅዳር እስከ ታኅስ 1967 ዓ.ም. የነበረው ወቅት ነው። በዚህ ወቅት ደርግ በአንድ በኩል በሐምሌ 2፣ 1966 ዓ.ም. መግለጫው፣ ‹‹(ደርግ) በኢትዮጵያውያን መሀከል ለብዙ ዘመናት የቆየውን በጎሳና በሃይማኖት የተመሠረተውን መለያየትና የኑሮ መራራቅ ‘ኢትዮጵያ ትቅደም’ በሚል ምነት፣ በብሔራዊ ስሜትና በኩልነት፣ ለአገር ዕድገትና መሻሻል ዓላማ ሕዝቡ ለሥራ ታጥቆ እንዲነሳና በዘመኑ ሥልጣኔ በይበልጥ ተካፋይ እንዲሆን የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋል፤›› የሚለውን አመለካከት አራመደ። በሌላም በኩል በኅዳር 1967 ዓ.ም.  ከጄኔራል አማን አንዶም ጋራ በተለይ በኤርትራ ጥያቄ በተፋጠጠ ጊዜ፣ “የኢትዮጵያ አንድነት ፍፁምነት” የሚለውን አመለካከት አራመደ። በወሩ በታኅስ 1967 ዓ.ም. “የኢትዮጵያ ኅብረተሰባዊነትን” ሲያውጅ ደግሞ፣ ‹‹የኢትዮጵያን አንድነት ለማጠንከር ብዙ መንገዶች አሉ፤›› ካለ በኋላ የሚከተሉትን ሁለት መንገዶች አሳወቀ

  • አገር ውስጥ ያለውን የባህሎችና የልዩ ልዩ ጎሳዎች መቀራረብ ይበልጡን ማጠንከር አንደኛው ዘዴ ነው። ኢትዮጵያ የአንድ ጎሳ ወይም የአንድ ባህል አገር አይደለችም። የተዛመዱ ልዩ ልዩ ነገድና ባህል የሚገኙባት አገር ናት። የዘለቄታ ጥንካሬዋ መሠረትም ይው ነው። ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብሮ በመኖሩ በጋብቻ፣ በባህል፣ በስሜትና በአስተሳሰብ ዝንባሌ፣ በቋንቋ ጭምር የተሳሰረ ነው። የአንድነትን ማጠንከር አንደኛው ዘዴ እንዲህ ያለውን የሚያስተባብር ነገር ሁሉ እንዲዳብር ማድረግ ነው። ዋናዎቹ ቋንቋዎች እንዲስፋፉ፣ ባህል ሁሉ እንዲያድግ፣ የሰው ሁሉ መብት እንዲጠበቅና የአገሪቱ ዜጋ ሁሉ በአንድነት ጥላ ሥር በፍቅርና በመተባበር እንዲሰባሰብ ማድረግ ያስፈልጋል
  • ‹‹ሁለተኛው መንገድ ደግሞ ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገሮች ጋር በተለይም ከሱዳን፣ ከሶማሊያና ከኬንያ ጋር ተባብራ የምሥራቅ አፍሪካ ብረተ ጉር እንድታቆም ማድረግ ነው›› ይህ አመለካከት ከደርጉ “ኢትዮጵያ ትቅደም” ዘመን መግለጫዎች ጋራ ሲነፃፀር የተሻለ ነበር። ደርጉም በዚሁ ጊዜ ታኅሳስ 14 የእስልምና ሃይማኖት ክብረ በዓሎችን ያካተተውን የብሔራዊ በዓሎች ዝርዝር አጥቶ ነበር። በታኅሳስ 18 ደግሞ፣ የአዲስ አበባ ራዲዮ ጣቢያ ለመጀመያ ጊዜ በኦሮምኛ ቋንቋ ፕሮግራሞችን ማስተላለፍ ጀመረ። ሁለተኛው ወቅት፣ የሕዝብ ድርጅት ጊዜያዊ ጽሕፈት ቤት በሚያያ 1968 ዓ.ም. ከተቋቋመ በኋላ ደርግ የብሔርን ጥያቄ ጨምሮ በተለያዩ የፖለቲካ ጥያቄዎች ላይ የአደባባይ ውይይቶች እንዲካሄዱ የመንግሥት መገናኛ ዘዴዎችን በከፈተበትና የውይይት ክበቦች በየ መሥሪያ ቤቱ ተቋቁመው እንዲወያዩበት በፈቀደበት ወቅት ጀመረ። 1968 ዓ.ም. በዚሁም፣ በብሔሮች ጥያቄ ላይ ይፋ ውይይቶች የተካሄዱበት ዘመን ሆኖ ተጠናቀቀ። ስተኛው ወቅት በሁለተኛው ወቅት ዘመን ከታኅስ 1968 ዓ.ም. አንስቶ እስክ የካቲት 1969 ዓ.ም. ድረስ በደርግ መሪዎችና በሕዝብ ድርጅት ጊዜያዊ ጽሕፈት ቤት አባል ድርጅቶች መካከል ረጅም ውይይቶች የተደረጉበት ወቅት ነበር። ደርግም የመጨረሻ መጨረሻ፣ “የራስ ገዝ አስተዳደር” የተባለውን የአስተዳደር መንገድ እስከ መቀበል ድረስ የሄደበት ወቅት ነበር።

ይሁን እንጂ፣ በ1969/70 የኢትዮጵያን አገር ወዳድ ተራማጆችና ምሁራን አጥፍቶና አግሎ ሥልጣንን ለመጠቅለል የበቃው የሻለቃ መንግሥቱ የመለዮ ለባሾችና ከፍተኛ ቢሮክራቶች ቡድን፣ በ1970 ዓ.ም. “የራስ ገዝ አስተዳደር” የተባለውን ትቶ፣ ‹‹አንድ ሰውና አንድ ጠብመንጃ እስኪቀር ድረስ፤›› ያለውን አካሄድ ያዘ። ይህም ሦስተኛው ወቅት ሲሆን ‹‹የምሥራቁን ድል በሰሜን እንደግመዋለን›› በሚል ጥሪ የኢትዮጵያን የብሔሮች ጥያቄ በጦር ኃይል “ለመፍታት” የሄደበት መንገድ ነበር። በኋላና ባለቀ ሰዓትም፣ “የብሔሮች ኢኒስቲቲዩት” የተባለውን ተቋም ወደ ማቋቋም ሄዶ ነበር። ጦርነቱ በግንቦት 1983 ዓ.ም. በኤርትራ ግንባሮችና በሕወሓት ኢሕአዴግ አሸናፊነት ተደምድሞ ሻለቃ መንግሥቱ ወደ ምባዌ ሸሹ። ኢሳይያስ አፈወርቂ በኤርትራ ነገሠ። የሕወሓት ኢሕአዴግ በአዲስ አበባ።  

የግድያና የጦርነቶች ዓመታት (1969 እስለ 1983)

የ1969 ዓ.ም. መጨረሻና የ1970 ዓ.ም. መጀመያ ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ አንድ አገር ወዳድና ተራማጅ ትውልድ በሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም መሪነት በተመለመሉ ገዳይ ቡድኖች ተጨፍጭፎ ያለቀበት ወራት ነበሩ። በዚሁም፣ የ1963’ቱ ውሳኔዎች ባለቤት የነበረው አገር ወዳድና ተራማጅ ትውልድ ከ1970 ዓ.ም. በኋላ በነበረው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ይወት ውሰጥ ይህ ነው የሚባል ሥፍራና ሚና ላይኖረው እስኪሆን ድረስ ተዳሞ አበቃ። ከ1970 እስክ 1983 ባለው የ13 ዓመታት ዘመን ዋና ተዋናዮች ሆነው የቀጠሉት ከላይ እንደተመለከተው ስለዚህም በአንድ ወገን በሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም መልማይትና መሪነት ከ1970 ዓ.ም. ጀምሮ የመንግሥትን ሥልጣን የጨበጠው የመለዮ ለባሾችና የከፍተኛው ቢሮክራሲ ቡድንና በሌላው ወገን የኤርትራ ግንባሮችና የተለያዩት የብሔር ድርጅቶች፣ በተለይም ሕወሓትና ኦነግ ነበሩ።

ሕወሓት ‹‹የኢትዮጵያ ዓይ ቅራኔ በብሔሮቿ መካከል ያለው ቅራኔ ነው፤›› ባለው የቅራኔ አረዳዱ ገፋ። ያም ከሌሎቹ የትግራይ ድርጅቶችና እስከ መንግሥት ሠራዊት፣ ከኢሕአፓ እስከ ኢዲህ ጋራ ድረስ ካሉት ኃይሎች ጋራ ተዋጋ። ሕወሓት ከተጠቀሱት ኃይሎች ጋራ ያካሄዳቸው ውጊያዎች ለሚታቁ አልመለስባቸወም። በዚሁ ዘመን “የኢትዮጵያን ቀኝ አገዛዝ” ሲዋጉ የነበሩት የኤርትራ ግንባሮችና ኦነግ የሄዱባቸው መንገዶችም ስለሚታወቁ እንደዚሁ አልመለስባቸም።

እንደዚሁም፣ ሕወሓት ከኢሕአዴግ አመሠራረት እስከ ኤርትራ ሬፈራንደም፣ ከሕገ መንግሥቱ መቀቅና መታወጅ እስከ “የፌዴራል” አስተዳደር አወቃቀር ድረስ የሄደባቸው መንገዶች ስለሚታወቁ አልቆይባቸውም። በአጭሩ፣ ኢሕአዴግ ከ1983 እስክ 2010 ዓ.ም. ድረስ አቶ መለስ ዜናዊ “አብዮታዊ ሞክራሲ” ባሉት አደረጃጀትና አመራር ለ27 ዓምታት ገዛ። እንዲያም ሲል ለ27 ዓመታት ሙሉ በአንድ ወገን የነፃ ገበያም ሆነ የመንግሥታዊ ካፒታሊዝም ባልሆነው “ካፒታሊዝም” ሲዘርፍ ኖረ። በሌላው ወገን፣ ፌዴራላዊ ባልሆነው “የፌዴራል አስተዳደር” ግዛቶችን ሲከልልና ሲያጥር ኖረ። ኦነግ በ1983 ዓ.ም. ሥልጣንን የተጋራ ቢሆንም ከጥቂት ወራት በኋል በሕወሓት ኢሕአዴግ ተገፍቶ ተሰናበ። ከዛም ከአሥር በማያንሱ ቡድኖች ተፋፍሎ በየውጭ አገሮች ሲንቀሳቀስ ቆየ።

ዳር 2010

ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአገሪቱ በመላ በተካሄዱት የተለያዩ ትግሎች የሕወሓት ኢሕአዴግ የሥልጣን ወንበር ተነቃነቀ። ሕወሓት ኢሕአዴግ በአንድ በኩል “ተድሶና ጥልቅ ተድሶ” እያለ በየ አዳራሹ ሲርመሰመና በሌላው በኩል ባስቸኳይ ጊዜ አዋጆችና ርምጃዎች ለመግታት ሲጥርበሁኔታዎች ተቀደመ። በመጋቢት 2010 ዓ.ም. ከሥልጣን ተገለለ። የሚያሳዝነው እንበልና፣ ሕወሓት የራሱ ኢሕአዴግ ጉባዔ ያደረሰበትን ሽንፈት ለመቀበል ተሳነው። በተቃራኒው፣ ወደ መቀሌ አፈግፍጎ ‹‹ሕገ መንግሥቴና የፌዴራል አስተዳደሬ ይነኩና፤›› እያለ ማስፈራራትንና መዛትን መረጠ። ኦነግ፣ አቶ ለማ መገርሳ ለየካቲቱ የኦሮሞ ጨፌ አምርረው እንደገለ‹‹እኛው (ኦሮሞዎች) በኛው (ኦሮሞዎች) ተጠላልፈን በፈጠርነው ችግር›› የኦሮሞን ሕዝብና አገሪቱን በችግር አጠላፎ ከማስቸገር ገባ። ሌሎቹም፣ ‘ከኔ በላይ የብሔሩ ወገን ለአሳር ነው’ በሚል ዓይነት አክርረው መለፍ ያዙ። ደግሞ ሌሎቹ፣ ፌዴራላዊ ወይስ አሃዳዊ በሚል ከንቱ ምልልስ ተጠምደው የሆነ ያልሆነውን እየተወራወሩ የሚደመጡ ሆኑ። ሌሎቹም፣ መብት የሚባለው ጉዳይ የሚሸራረፍ ግዑዝ ዕቃ የሆነ ይመስል፣ በዜግነትና በቡድን መብቶች እየበቱት የተከታዮች መቀስቀሻና የደጋፊዎች ማበራከቻ መሣሪያ አድርገው መወናኘት ያዙ።

የኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄ ከየት ወት እንደተጓዘ በመጠኑ ለማቅረብ ሞክሬአለሁ። እያወቁም ቢሆን በ60’ዎቹ የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን ላይ የሚዘምቱትን ምንም ለማረግ አይቻልም። ባለማወቅ ለሚያትቱት ግን መጠነኛ መረጃ እንደቀረበ ተስፋ አደርጋለሁ። ነገር ግን አንዳንዶች ዛም፣ የ60’ዎቹን የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን የትግል ታሪክ ወደ “እናፋለን ወይም እናሸንፋለን” አውርደው ሲያትቱ ይደመጣሉ። እነዚህ ክፍሎች የትውልዱን የትግል ታሪኩ በውል ቢያስተውሉ ግን የ60’ዎቹ የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን “እናቸንፋለን ወይም እናሸንፋለን” ያሉና “ወዝ ላብ አደር” ያሉ ቢሆኑም የተለያዩት በነዚህ ቃላቶች ምክንያት እንዳልሆነ ባስተዋሉ ነበር። የተለያዩት በወቅታዊ ሁኔታ ምንባባቸውና ትንተናቸው፣ በቅራኔዎች አቀማመጥና በኃይሎች አላለፍ አረዳዳቸውና ለትግላቸው በመረጡት የትግል ልት ነበር። ከዚህም በተያያዘ ስለየራሳችው አቅም በነበራችው የገዘፈ ወይም የተመዘነ አተያይ ነበር። 

አተኩረን ብንመለከት፣ በዛሬዎቹ የፖለቲካ ተዋናዮች መካከል ያሉት የዛሬው ልዩነቶችም በዋናነትና በመሠረቱ በነዚሁ ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶች ናቸው። በኔ ዕይታ ስለዚህም የተመለቱትን የራስ ጉዳዮች በአንክሮ ከማጤንና ከማስተዋል እንጂ “እናቸንፋለን ወይም እናሸንፋለን” ይባል የነበረውን እየደጋገሙ ለዛሬ ቅስቀሳና ለዛሬ ድጋፍ ማጋበሻ መጠቀም ለዛሬውም ሆነ ለወደፊቱ የሚጠቅምን ትምህርት አያስገኝም። እንደውም ለማለት ይቻላል አካሄዱ የትላንትናውን ቀርቶ የዛሬውንም በውል ለመረዳት አይረዳም። ለነገውም አይበጅም።

የ60’ዎቹ የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን እንደዚሁም፣ አንድ የርዕዮተ ዓለም አመለካከትና ምነት የነበራቸው ቢሆኑም መግባባትና መተባበር ተኗቸው ተጠፋፉ በሚል ይወቀሳሉ። ስለመጠፋፋታቸው የሚደረገው ወቀሳ በወል የተጠና ባይሆንም በጥቅሉ አግባብነት አለው። ይሁንና አሁንም አተኩረን ብንመለከት ግን አንድ ርዕዮተ ዓለም (ሃይማኖትንም ጨመሮ) ለመስማማትና ለመተባበር ዋስትናን የሚሰጥ መያዣ አይደለም። ሲጀመር ፍልስፍና፣ ምነት፣ ርዕዮተ ዓለም፣ ፖለቲካ. . . ሁል ጊዜም አከራካሪ ናቸው። ሰዎች ወይም ቡድኖች አንድ ዓይነት የርዕዮተ ዓለም ሆነ የሃይማኖት ምነት ቢኖራቸውም  በትርጉምና በትንታኔ መለያየትና መጋጨት በመላው ዓለም ሁሌም የነበረ፣ ያለና ሁሌም የሚኖር ነው። በአገራችንም በ15’ኛው ክፍለ ዘመን በአባ እስጢፋኖስ ደቂቃን ተከታዮችና በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ መንግሥት ካህናት መካከል የከረሩ ልዩነቶች ነበሩ። በ19’ኛው ክፍለ ዘመን በተዋህዶ አማኞች ዘንድም ሦስት ልደት፣ ሁለት ልደት፣ ካራ. . . በሚባሉት ተከታዮች መካከል የከረሩ ፍጭቶች ተካሂደዋል።

በ17’ኛው ክፍለ ዘመን አውሮፓም በካቶሊክና በፕሮቴስታንት ክርስያኖች መካከል የ30 ዓመታት ጦርነቶች ተካሂደዋል። በእስልምና አማኞች ዘንድ በሱኒና በሺያ ተከታዮች መካከል አስከ ዛሬ ያልበረደ ግጭት ይካሄዳል። ወደ ማርክሲዝም ስንመጣ በሌኒንና ፕሌካኖቭ፣ ቡካሪንና ካውትስኪ፣ በስታሊኒስቶችና ትሮትስካይቶች፣ በቻይናና ሶቪየት ብረት፣ በአልባኒያና ቻይና፣ በኤይሮ ኮሚዮኒዝምና ሶቪየት ብረት. . . መካከል የተካሄዱትን ለማስታወስ ይቻላል። በኢትዮጵያ አብዮት ዘመን ‹‹ያንኑ አንድ የማርክሲዝም ርዕዮተ ዓለም ይከተሉ የነበሩት›› ታጋዮች የተለያዩት ዙሮ ዙሮና አሁንም ግን፣ የወቅቱን ሁኔታ በማርክሳዊ የትንተና ዘዴ ተንትነው በደረሱበት ድምዳሜና በቀየሱት የትግል ልት ስለተለያዩ ነበር።

በሌላ አገላለ እስከ መጠፋፋት የደረሱት ይቁኑ፣ የሌላውን ሳብና አስተሳስብ በማክበር ባህል ያልበለጉ ስለነበሩ ነበር። ወይም፣ የሲቪክ ባህል ጉድለታው ከፍተኛ ስለነበር ነበር። እንዲያም ሲል፣ ከፖለቲካ ድርድርና ከሰጥቶ መቀበል የፖልቲካ አመራር ባህልና ሥዓት ሩቅ፣ እጅግ በጣም ሩቅ ስለነበሩ ነበር። የዛሬዎቹ የፖቲካ ተዋናዮች ስለዚህም በዚህ ረገድ ያውን ጉዳይ አሁንም ከስሜታዊ መግለጫዎችና ውግዘቶች ወጥተው ጉዳዩን በጥሞና ቢያጤኑት ለዛሬውና ለነገው የሚቅም ትምህርት ሊገኝ ይችላል። ዛሬ በተለያዩ አካባቢዎች በተለያዩ የፖለቲካ ጥያቄዎች “በይዋጣልን” ዓይነት ተፋጠው የሚገኙት የዛሬዎቹ የፖቲካ ተዋናዮች ይህቺን ትምህርት ቢቀስሙ ከታሪክ ሚነት ይተርፉ ነበር። ከ60’ዎቹ የኢትዮጵያ ተራማጆችና ምሁራን ልቀው ለመገኘት የበቁ ይሆኑ ነበር።

ኢትዮጵያ ከ2010 ዓ.ም. በኋላ ከመቶ የማያንሱ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚርመሰመሱባት አገር ሆናለች። ይሁንና፣ የመዎቹ ጥቂት ወራት ዕጣዋ የሚወሰነው በአንድ ወገን አዲስ አበባና መቀሌ በሚሄዱበት ወይም በማይሄዱበት መንገድ ነው። በሌላው ወገን የየክልሉ የማንነት፣ የወሰንና የከተሞች ተሟጋቾች በሚሄዱበት ወይም በማይሄዱበት መንገድ ነው። እነዚህ ናቸው በመዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ከማንም በላይ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች ክፉ ሊደግ የሚችሉት። ከማንም በላይ ሰክነውና ልብ ገዝተው በነቷ የፈካች የአዲስትና ሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ መሥራች አባቶች ለመሆን የመብቃት ዕድል ያላቸው።

ከማንም በላይና ይልቁኑም ደግሞ፣ ለኢትዮያ ከስድስትዮን በላይ ለረብ ተጋላጭ ወገኖች፣ ለሦስት ሚልዮን ተፈናቃዮች፣ ለሚዮን ሥራ አጦችና በችጋር ደመወዝ ለሚማቅቁት የኢትዮጵያ ወዝ ወይም ላብ አደሮች ለመድረስ መትጋት ያለባቸው። በየ ቴሌቪን መስኮቱ እንደሚታየው፣ የዋሳ ንዱስትሪ ፓርክ በጎቢኚዎች ይጨናነቃል። ይሁንና፣ የዛሬዎቹ የፖቲካ መሪዎችና ተዋናዮች ላውራዲን የተባለችውንም ጎብኚ ቢያደምጡ፣ “ሕዝብ ተኮር” የሚሉት የማኅበራዊ ኢኮኖሚ አመራር “ሕዝብ ተኮር” እንዳልሆነ ይረዱት ነበር (Laura Dean Ethiopia Touts Good Conditions in Factories for Brands Like H&M and Calvin Klein, but Workers Scrape By on $1 a Day‚ The Intercept‚ July 8 2018) ሞክራሲ፣ ሰዓዊ መብት፣ ሶሻል ሞክራሲ እያሉ ዙ የሚናገሩት የተቃዋሚ ፍሎችም፣ በተጨባጭ ለተገፉት የቆሙና የሚታገሉ በሆኑ ነበር።

የኅዳር 2010 ዓ.ም. የሥልጣን ባቤቶች፣ የዛሬው የፖቲካ መሪዎችና ተዋናዮች በኢትዮጵያ ብሔሮች ጥያቄ ላይ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ከተሄደባቸው መንገዶች ተምረውና ታርመው፣ ለፖለቲካ የሰጥቶ መቀበል ድርድርና ስምምነት እንዲበቁ ተስፋ ይደረጋል። “ለይዋጣልን” እየቀረቀቡ የሚገኙት ወገኖችም ሰክነውና ልብ ገዝተው ወደ ቲካ ውይይትና ድርድር የመመለስ ብሔራዊ ወይም አገራዊ ግዴታ አለባቸው። በያዙት መንገድ ከቀጠሉ ግን፣ ለብሔራቸውም ሆነ ለአገራቸው ክፉውን ደግውና ፈመው የሚያልፉ የሺ ዘመናት ተወቃሾች ይሆናሉ። የኢትዮጵያ ሕዝቦችና ኢትዮጵያ አሁንም በፖቲካ ኃይሎቿ የታሪክ ሽሚያና “መጠላለፍ” ለሌላ ዙር ጦርነት ተዳርገው፣ ደግሞ ደግሞ የሌላ ዙር ጥፋትንና ውድመትን የሚሸከሙበት ትከሻ የላቸውም። ድዋው ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ከዛሬ 110 ዓመት በፊት “አፄ ምኒልክና ኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በደረሱት መሐፍ ውስጥ፣ ‹‹ምስኪን ኢትዮጵያ! የዕድልሽ ቀን መች ይነጋ ይሆን?›› ብለው ጠይቀው ነበር። የ2011 ዓ.ም. ኢትዮጵያ የፖልቲካ ኃይሎች የአዲት ኢትዮጵያ መሥራች አባቶች መሆንን ከመረጡ ኢትዮጵያ የነጋድራስን ጥያቄ ከ110 ዓመታት በኋላ መሶ የሚያቀርብ ሌላ ገብረ ሕይወት የሚያስፈልጋት አትሆንም።

 ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...