Friday, June 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉየታሪክ ሥፍራችንና የጋራ ወደፊታችን

የታሪክ ሥፍራችንና የጋራ ወደፊታችን

ቀን:

በአንዳርጋቸው አሰግድ

የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሪዎችና ተዋናዮች አምርረው የሚመላለሱበት አንድ ጥያቄ ስለታሪክ ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን የታሪክ ጥያቄዎችን ለታሪክ ባለሙያዎች ትተን ወደ 21ኛው ክፍለ ዘመን ለመሻገር የተቸገርነው አንድም፣ ታሪክ ቢወደድም ቢጠላም ፖለቲካዊ ስለሆነም ነው። ስለሆነም ነበር የኢትዮጵያ ነገሥታት ሊቃናትንና መነኮሳትን እያስመጡ መዋዕለ ዜናቸውን ሲያፉ የኖሩት። ሊቃናቱና ኮሳቱም፣ የተረኛውን ነጋሢ አንጋሽና አወዳሽ ዝክር ሲፉ የኖሩት። ስለነበረም ነው የብሔር እንቅስቃዎች ወደ ፖለቲካው መድረክ ከመጡበት ከ1960ዎቹ ወዲህ የፖለቲካ ግባቸውን ለማራምድ የየራሳቸውን ትርክት ወደ ማሳወቅ የተሻገሩት። ስለዚህም ደግሞ እንኳን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ የተመሠረተችው ኢትዮጵያ ያቀፈቻቸው የመላ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ታሪክ ቀርቶ የቅድመ አፄ ኒልክ የስድስትም ይሁን የአምስት ወይም የስት ሺ ዘመን ትርክት የሚያነታርከው።

ፖለቲካዊው ትርክት በተለይ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ በተካሄደው የአፄ ምኒልክ መስፋፋት ዝክር ላይ ያተኮረ የነበረውን ያህል ምልልሱ ነጋሶ ጊዳዳ (ዶ/ር) በመጋቢት 13 በተካሄደ አንድ ስብሰባ ላይ ‹‹የኢትዮጵያ ብሔተኞች›› ባሏቸውና ‹‹የብሔር ብሔተኞች›› ባሏቸው ክፍሎች መካከል እየሆነ ሄደ። በምልልሱ አንዱ ክፍል ምኒልክን ላያስነካ ገትሮ እንደሞገተ ስድሳ ዓመታት ተቆጠሩ። ሌላው ክፍል ተገቢ የመብት ጥያቄዎችን ይዞ የተነሳ ቢሆንም ቅሉ የአፄ ምኒልክ መስፋፋት ባደረሰው በደልና ሰቆቃ ታሪክ ላይ ተወስኖ እንደሞገተ ስድሳ ዓመታት ተቆጠሩ። ውይይቱ/ክርክሩ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ተከንችሮ የቆመውንም ያህል ‹‹ትምክህተኛ›› እና ‹‹ጠባብ››‹‹የአንድነት›› እና ‹‹ገንጣይ/አስገንጣይ›› ኃይል እየባባሉ ተካረሩ። ስለጋራ ወደፊት ለመወያየት መቀራረብና መደራደር አቀበት ሆነ።

በሁለቱም በኩል የሚያስገርመውና የሚያሳዝነው እስከዚህም የደረሱትን በደሎችና ሰቆቃዎች አንዱ በማሳነስና ሌላው በማጉላት መሟገታቸው አይደለም። ይልቁንም ለፖቲካ ግባቸውና ተከታይን ለማበራከት ሲሉ የታሪክንና የማኅበራዊ ክንዋኔን ትንተናን ለማፋለስ እስከ መድፈር ጭምር መሄዳቸው ነው። ከዚህም በባሰ ደግሞ የዛሬው ታሪክ ሠሪዎች እነሱው ቢሆኑምና ትኩረታቸውን የሚጠይቁ በርካታ አጣዳፊ ጉዳዮች ከፊታቸው ያሉ ቢሆንም ቅሉ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አፄ ምኒልክ ኢትዮጵያ ላይ ሲመላሱና ሲወነቻቸፉ የሚያባክኑት ጊዜና ጉልበት ነው። የባሰውን የሚያሳስበውና የሚያስደምመው ደግሞ በ20ኛው ክፍለ ዘመን በተገኙት መሠረታዊ ለውጦች ላይ ቆመው፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ መሐንዲሶች ለመሆን በጋራ አለመትጋታቸው ነው።

ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ የ2011 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ሰው ቢሆኑ ከ100 ዓት በፊት ከፉት ሐተታ አንድም ቃል ሳይለውጡ ሑፋቸውን ለድጋሚ ዕትም ይሰጡት ነበር። በንባቡ የበረታ የ2011 ዓ.ም. አንባቢ ከሑፋቸው የሚከተለውን ሲያገኝ ደግሞ እኛ ኢትዮጵያዊያን በውነት 21ኛው ክፍለ ዘመን ገብተናል ወይስ አልገባንም በማት ራሱን አምርሮ ይጠይቅ ነበር። የሚከተለው ነው፡፡

‹‹ኛ የኢትዮጵያዊያን ያለፈው ታሪክ እጅግ ያሳዝናል። ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ እስካሁን ድረስ ፍፁም የሆነ ሰላም አግኝተን አናውቅም። የተወደደች አገራችን ዘወትር በጠላቶች ተከባ ስትኖር ነበረች ትኖራለችም። ነገር ግን የውጭ ጠላት ከዚህ በፊት አላዋረደንም። አንድነትም ስንሆን ምንም የሚደፍረን እንደሌለ ታሪክ ይመክራል። ዘወትርም በስምምና በፍቅር አድረን ብንሆን እስከ ዛሬ ድረስ ብዙውን ትልልቅ ነገር መፈም እንችል እንደነበር ጥርጥር የለውም። እግዚአብሔር ብዙ በረከት ሰጥቶናልና። ትምርትን በቶሎ መቀበል የሚችል ልቦናና የጦረኛን ባህሪ ማለያና ሀብታም አገርንም። ካለመስማማታችን የተነሳ ግን … ወደ ኋላ ቀረን …።

‹‹ሮውም የአንም ኑሯችን እጅግ ያሳዝናል። በመላው ዓለም ላይ ሰላም ሲሰፋ አዕምሮም ስትበራ እኛ በጨለማ እንኖራለን። እርስ በርሳችን መጠራጠርንም አልተውንም። ሕዝቦቹ ሁሉ እርስ በርሳቸው በፍቅር ተቃቅፈው ስለልማታቸው በአንድነት ነው ሲደክሙ እኛ አንድ ዘርና ወንድማማች መሆናችንን ገና አልተገለልንም። እርስ በርሳችን መፋጀትም እስከ ዛሬ ድረስ ጀግንነት ይመስለናል። ስለዚህም እግዚአብሔር ለብርታት የሚሆነውን ስጦታ ሁሉ ሰጥቶን ሳለ ባለቤቶቹ ነፍን። ሌሎቹም ነገሥታት እንደ ነፎች ይቆጥሩናል፡፡ ይንቁልም፤›› (ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ፣ አፄ ምኒልክና ኢትዮጵያ፣ 1902)።

ነጋድራስ ከመቶ ዓመታት በፊት ‹‹እርስ በርሳችን መጠራጠርንም አልተውንም›› ያሉት ባሪይ፣ ከፖለቲካዊ ትርጉሙ አንፃር የኢትዮጵያን ሕዝቦች በማመልከት አይደለም። ይልቁኑ ገዎቿንና ልቃኑን በማመልከት ነው። ለዛሬው ሁኔ ብናውለው ዶ/ር ነጋሶ ‹‹የኢትዮጵያ ብሔረተኞች›› እና ‹‹የብሔር ብሔተኞች›› ያሏቸውን ክፍሎች ማለት ይሆናል። የትንቷና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ መሪዎች፣ ተዋናዮችና ምሁራን ነጋድስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ገና በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የሰጡትን ‹‹(በፖለቲካ) ስምምና (በሕግ የበላይነት) ፍቅር አድረን ብንሆን….›› ሮ የኢትዮጵያን የፖቲካ ሜዳ በኢትዮጵያ የፖቲካ በሬ አሳምረው ለማረስ የበቁና የሚበቁ በሆኑ ነበር።

ለቡድን መብት የሚታገለው ክፍል ‹‹የኢትዮጵያ ብሔተኛ›› የተባለውን ክፍል ‹‹የቀድሞውን የብሔር ጭቆና መልሰህ ልታመጣ!›› እያለ ይጠረጥረዋል። ለዜግነት መብት የሚታገለው ክፍል ‹‹የብሔር ብሔተኛ›› የተባለውን ክፍል ‹‹አገር ልትከፋፍል!›› እያለ ይጠረጥረዋል። አተኩረን ብንመለከት ግን ሁለቱ ወገኖች ለመተማመን በመቸገራቸው እንጂ ልዩነትን እያገዘፉ ጥያቄውን የተከታዮ ማበራከቻ መሣሪያ ስላደረጉት እንጂ እንዲያም ሲል የሥልጣን መወጫ መሰላል ስላደረጉት እንጂ የዜግነትና የቡድን መብቶች የማይነጣጥሉ ሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው። በሞክራሲያዊ ሕግና ሥዓት መንገዶች የሚታረቁ መብቶች ናው።

ዳዊ ወይስ ፌዴራላዊ አስተዳደር በሚለው ላይ የሚካሄደውም ምልልስ ለተከታዮች ማበራከቻ እየዋለ ተወሳሰበ እንጂ የ2011 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ‹‹ልዩነት›› ኖ ሊያመላልስና እርስ በርስ ሊያጠራጥር ባልተገባው ነበር። አዳዊ አገዛዝ በኢትዮጵያ ምድር ላይመለስ ታሪክ ኖ አልፏል። በዛሬይቱ ኢትዮጵያ በልበ ሙሉነትና ሽንጡን ገትሮ ለአዳዊ አስተዳደር የሚሞግት ወገን ሥፍራ የለውም። የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ ፖቲካ መሪዎችና ተዋናዮች ተግባርና ኃላፊነት ይልቁንም ኢሕአዴግ ተግባራዊ ያላደረገውን ፌዴራሊዝም በሰጥቶ መቀበልና በወደፊት ተመልካች ውይይትና ድርድር በተግባር ፌዴራላዊ ማድረግ ነው። የኢትዮጵያ የሆነን የቆንጆ ፌዴራሊዝም መሥራች አባቶች ለመሆን የመሥራትና የመብቃት ነው።

ወደ ርዕሱ ለመመለስ ነጋድራስን የቀደሙ የሞክራሲ መብት አስተማሪዎችም ነበሩን። ለዚህም የአውሮዊያን ዘመነ አብርሆት (Period of Enlightment) መራቾች ተብለው ከሚታወቁት ዴሰካር፣ ሎክ፣ ካንትና ቮልቴር በፊት ስለሰብዓዊ መብትና የፆታ ኩልነት በተሻለ የተመራሩትና ያስተማሩት የኛው የ17ኛው ክፍለ ዘመን የጎንደሩ እንፍራዝ ፈላስፋ ዘርዓ ያዕቆብ (ወርቄ) እና ተማሪያቸው ወልደ ሕይወት ናቸው። እነሱ ነበሩ፣ ‹‹ሰዎች ሁሉ ኩል ናቸው››፣ ‹‹ፆታዎች ኩል ናቸው›› የሚሉትን የሰብዓዊ መብት መርህና አቋም ሐተታ በተሰኘው ድርሰታቸው ውስጥ ያወጁት (Dag Herbjørnsrud the African Enlightenment 2016)። ወደየብሔሩ ቤት ገብተን ብንጠይቅ ተመሳሳይ አመለካቶች ይገኛሉ።

ዳግ ሄርብዮርንስሩድ ቀጥሎ እንሚለው ‹‹የአውሮውያኑ ዘመነ አብርሆት ወደ ፖለቲካ በራዊ እንቅስቃሴ አደገ። ለሰብዓዊና ሞክራሲያዊ መብቶች ለተደረገው ትግል ፈር ቀደደ። የ ዘርዓ ያዕቆብ ግን ወደ ፖለቲካ በራዊ እንቅስቃሴ ለማደግ ሳይታደል ቀረ››፡፡ ስለዚህ ግን እነ ዘርዓ ያዕቆብ ገና ከ300 ዓመት በፊት የተሟገቱለትን የሰው ልጆች ሞክራሲያዊና ሰዓዊ የኩልነት መብት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊያን በዚህና በዚያ ምክንያቶች (ሰበቦች) ለግለሰብ ዜጋ ይሁን ለብሔር የማያውቁበትና የሚገድቡበት ምክንያት የለም። ከ300 ዓመታት በኋላም ቢሆን ተግባራቸውና ኃላፊነታቸው ይልቁንም የኢትዮጵያን ዘመነ አብርሆት ጎህ ማብራት ነው።

ታሪክ ከየት እንደመጣን የሚገልልን የትንት ሥረ መሠረት ነው። የዛሬውን ለመረዳት የሚያግን የትምህርት ገበታ ነው። መደገም የሌለባቸውን የታሪክ ሰቆቃዎችና ግድፈቶች ዘርዝሮ የሚያቀርብልን መስተዋት ነው። አኩሪ የታሪካችን ገችም እንደዚሁ፣ የዛሬውን ለመረዳት የሚያግዙን የትምህርት ገበታዎች ናቸው። የዛሬውና የወደፊቱ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች በሚጠይቁት ልክ እንድንደጋግማቸው የሚያነሳሱን የታሪክ ቅርሶቻችንና ሴቶቻችን ናቸው። ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ በተጠቀሰው መሐፋቸው አሁንም በጥሩ እንዳስተማሩት፡፡

‹‹ታሪክን መማር ለሁሉ ይበጃል። የታሪክ ትምህርት የሚጠቅም ግን የእውነተኛ ታሪክ ትምህርት ሲሆን ነው። እውነተኛ ታሪክን መፍ ግን ቀላል አይደለም። ስት የእግዚአብሔር ስጦታዎች ያፈልጉናልና። እነዚህም ተመልካች ልቦና፣ የተደረገውን ለማስተዋል የማያዳላ አምሮ፣ በተደረገው ለመፍረድ የጠራ የቋንቋ አገባብ፣ የተመለከቱትንና የፈረዱትን ለማስታወቅ። የአገራችን የታሪክ ሐፊዎች ግን በነዚህ ነገሮች ላይ ኃጢት ይሠራሉ። በትልቁ ነገር ፈንታ ትንሹን ይመለከታሉ። ለእውነት መፍረድንም ትተው በአድልኦ ልባቸውን ያጠባሉ። አጻጻፋቸውም ድብልቅልቅ እየሆነ ለአንባቢ አይገባም፤›› ይላሉ፡፡

በሌላ አገላለ ታሪክ ሙያውን በተካኑና በነጋድራስ ቃል ‹‹የማያዳላ ምሮ›› ባላቸው ምሁራንና ቃን በየዘመኑ ውስጥ በአግባቡ እየተካተተና በማስረጃ ተመክሮ ሲተረክ ነው የጎደለው የሚሟላው። የተዛነፈው የሚቃናው። የተጣረሰው የሚታረመው። ድክመቶች የሚለቀሙት። ጥንካሬዎች የሚነቀሱት። ልዩነትና ተመሳሳይነት የሚጎሉት። በየጊዜው የተከሰቱት ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች የሚተነተኑት። መስተጋብሮች የሚገለት። ተወራራነቶች የሚንፀባረቁት። የጋራ ሴቶችና ፀጋዎች የሚደሩት። የትምህርት መቅሰሚያ ገበታነቱ የሚደምቀው። የጋራ ሥረ መሠረት የሚጠናከረው። ከታሪክ ጋራ መታረቅና ብሔራዊ/አገራዊ ወደፊት ተመልካችነት የሚዳብረው። ለኢትዮጵያ ሕዝቦችና ብሔሮች የጋራ ወደፊትና ለብሔረ መንግሥት (Nation State) መገንባትና መደርጀት የሚያስተሳስረው። የሚያስተባብረው። የጋራ ወደፊትን የሚያፀናው።

ታሪክ ከላይ እንደተመለከተው ቢወደድም ቢጠላም ፖለቲካዊ ነው። በኢትዮጵያ ግን አክርሮና ተካሮ በአሁኑ ወቅት ተቃርኖና ተፃርኖ የሌለበት አንድም የታሪካችን ገ የለም። አቶ ኢብሳ ጉተማ ከዛሬ ምሳ ዓመት በፊት ‹‹ኢትዮጵያዊው ማነው?›› ብሎ በግጥም ያቀረበው ጥያቄ የዛሬም ጥያቄ ሆኖ ያመላልሳል። እንዲያውም ለማለት ይቻላል፡፡ በዛሬው ወቅት አንዳንድ ንፈኞች የሚሄዱበት መንገድ ወስዶ ወስዶ መቋጠሪያው ከሚያጥር ሁኔታ ውስጥ እንዳቀረቅር ያጋል። በሌላው በኩል ዛሬ አፍጠውና አግጠው ያሉት በርካታ የፖለቲካና የማኅበራዊ ጥያቄዎች አስቸኳይ የጋራ መልሶችን ይፈልጋሉ። የዛሬው የፖቲካ መሪዎች ስለዚህም በአስቸኳይ ሰብሰብ ብለው በአንድ በኩል በንፈኞች እየተጠለፈ ያለውን የፖለቲካ ድባብ በአስቸኳይ መግታት አለባቸው። በሌላው በኩል ለአንዳንድ አስቸኳይ የፖለቲካ ማኅበራዊ ጥያቄዎች አስቸኳይ መልሶችን መስጠትና በተግባር ማሳየት አለባቸው።

ኔ ዕይታ ለዛሬው ሁኔታ የሚበጀው ምናልባት ለአዎንታዊ ለውጥና ለጋራ ወደፊት የቆመው ክፍል የታሪክን ጉዳይ ከዛሬው የፖለቲካ ምዕራፍ ምልልስ ውስጥ ለማስጣት ቢስማማ ነው። በዚህ ስምምነት መሠረትም በአንድ በኩል በዛሬው አጣዳፊ የፖለቲካ ማኅበራዊ ጥያቄዎች ላይ አትኩረው ሊሠሩ ይችላሉ። በሌላ በኩል የጋራ ወደፊት ግንባ መሪነትና አስተማሪነት ሚናቸውን በጋራና በአግባቡ ለመጫወትና ለመወጣት ይችላሉ።

የመሪ አስተማሪነት ሚናቸው በሦስት ዓይ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ቢፈ ሜታው ከፍተኛ ይሆናል ዬ እገምታሁ። አንደኛ በታሪክ ጠባሳዎች ሥፍራ ላይሁለተኛ በክፉና በጎ የጋራ ትውስታዎች ሥፍራ ላይ፣ ሦስተኛ በጋራ ወደፊት ሥፍራ ላይ። በሚከተሉት ፍሎች በነዚህ ጉዳዮች ላይ አተኩሬ አንዳንድ ሳቦችን ለማቅረብ እሞክራልሁ።

የታሪክ ጠባሳ ያልታተመበት አንድም ኅብረተሰብ የለም

ክሎድ ሌቪ ስትራውስ በጥሩ መንገድ እንዳሉት፣ ‹‹ከዝቅተኛው ማበረሰብ አንስቶ የታሪክ ሁነቶች ጠባሳ ያልታተመበት አንድም ኅብረተሰብ የለም›› (“There is no society, however primitive, which does not bear the ‘scar of events”, Claude Levi Strauss, Structural Anthropology, 1968) ታሪካችንን በዚህ መነር ብንመለከተው፣ ከኢትዮጵያ የረም ዘመን ታሪክ ውስጥ ሺ የታሪክ ጠባሳዎችን ለመደርደር ይቻላል። ሺ የሕዝቦቻችንን ሰቆቃዎች ለመደርደር ይቻላል።

ከቅድመ አክሱማያዊንና አክሱማያዊን ወታደራዊ ዘመቻዎች እስከ ዮዲት ከሦት ክ ዘመኑ የክርስቲያንና የእስላም ኢትዮጵያ ጦርነቶች እስከ የኦሮሞዎች የሰሜን፣ ምሥራቅና ምዕራብ ጉዞከዘ ፍንት የመቶ ዓመት ግጭቶች ስከ ቴዎድሮ ፀረ ካህናት ድጊቶች፣ ከቴዎድሮስ፣ ከዮሐንስና አሉላ ሔራዊ ነፃነት ትግል ከቴዎድሮስ ፀረ ካህናት ድርጊቶች እስከ ዮሐንስ ፀረ እስላም ድርጊቶች በአፄ ምኒልክ የደቡብ ዘመቻ ወቅት ከተፈመው ሰቆቃ እስከ ድዋ ከሰገሌ ጦርነት የአፄ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት እስካፈነው የባለ መሬቶች አገዛዝዋይ ወንድማማቾች የ1953 ዓ.ም. የቤተ መንግሥት ርሸና እስከ የደርግ የ1960ዎቹ ርሸና ከነጭ ሽብር እስከ ሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማር ቀይ ሽብርና እስከ ‹‹አንድ ሰውና አንድ ጠብመንጃ እስኪቀር ድረስ›› የነበሩትን ሰቆቃዎችና ጠባሳዎች ሁሉ ለመቁጠር ይቻላል። ዛሬም የሚዮኖች መፈናቀል ያተማቸውን ጠባሳዎች ለማከል ይቻላል….

ሌቪ ስትራውስ ‹‹የሁነቶች ጠባሳ ያልታተመበት አንድም ኅብረተሰብ የለም›› ሲሉ፣ ስለዚህም የታሪክ ጠባሳ ነገር አይነሳ ማለታቸው አይደለም። የታሪክ ጠባሳዎች በተገቢ የሚነሱ ቢሆንም ቅሉ ታዋቂው የታሪክ ምሁር ፌርናን ብሮዴል አስከትለው እንዳሉት፣ ‹‹የአጭር ጊዜ ሁነቶችን (History of Short Events) ከዘመን ተሻጋሪ ክንዋኔዎች (Long Lasting Movements) ሳይታክቱ መለየት ያስፈልጋል፡፡ ማለት ነው (At each moment, one has to distinguish between long-lasting movements and short bursts”, Fernand Braudel On History 1982)  

በሌላ አገላለ የፖለቲካ ተዋናዮች በታሪክ ዓይንና ሚዛን የአጭር ጊዜ የሆኑትን ሁነቶች ለፖለቲካ ግብ ማራመጃ ሲጠቀሙባቸው ታሪክ ከታሪክነት ይልቅ ፍርድ ቤት ይሆናል። የደጋፊ ማበራከቻና የሥልጣን መጨበጫ መሣሪያ ይሆናል ማለታቸው ነው። የኢትዮጵያ ታሪክ አተራረክ የአጭር ጊዜ ሁነቶች የተውትን የታሪክ ጠባሳዎች ከሚደርደርና ርሾ ከሚያቋጥር አተራረክ ተላቆ የሕዝቦቿን ዘመን ተሻጋሪ የጋራ ትውስታዎች (Shared Memories) የሚተርክ ቢሆን የሕዝቦቿን የጋራ ወደፊት ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት በብዙ ክንድ ለማቀራረብና ለማቅለል ይቻላል ማለት ነው። የዛሬዎቹ የፖለቲካ መሪዎችና ተዋናዮች ከታሪክ ጠባሳዎች ይልቅ የኢትዮጵያን ሕዝቦች ፉና በጎ የጋራ ትውስታዎች አጉተው የሚያስተምሩ ቢሆኑ የሕዝቦቿን የጋራ ወደፊት መሠረት ያደደሉ መሪዎች የመሆን ዕድል አላቸው።

በየነገሥታቱ መዋዕለ ዜና ጠባቂዎች ይፉ የነበሩት የየነገሥታቱ ታሪክ በነጋድራስ ገብረ ሕይወት ግሩም አባባል ‹‹የንጉሡን እንጂ የሕዝቡን ጥቅምና ጉዳት አይቆጥሩም›› ነበር። ስለዚህም ስለነገሥታቱና ስለመሳፍንቶቹ እንጂ ስለሕዝቡ ታሪክ (Peoples History) የተላለፈልን ወይም የተጠናውና በሑፍ የቀረው ትንሽ በጣም ትንሽ ነው። የጀርመኑ ገጣሚና ድራማቶግ ቤርቶልት ብሬሽት ‹‹ሄር ካ›› በተባለው ስብስቡ ውስጥ ‹‹(እገሌ) ይንና ያንን ጦርነት አሸነፈ›› ይባላል። ፈሱን ው ያጠጣለት ሰውም አልነበረም ወይ? መጫሚያውን የወለወለ ሰውም አልነበረም ወይ? ግብ ያበሰለለትም ሰውም አልነበረም ወይ?›› እያለና የታወቁ ነገሥታቶችንና ጄኔራሎችን ዝክር እያታወሰ ብዙ ይጠይቃል።

የስድስትም ይሁን የአምስት ወይም የስት ሺ ዘመን ጦርነቶችንና የሕዝቦች ንቅናቄዎችን የኢትዮጵያ አርሶና አርብቶ አደሮች፣ ነጋዴዎች፣ አንረኞች፣ ፋቂዎች፣ ፃናት፣ ጎልማሶች፣ ሽማግሌዎች፣ እናቶች… እንዴት ኖሩት? እንዴት አለፉት? ብሎ የጠየቀ የታሪክ ድርሰት የለንም። የታሪካችን ትርክት ይብዛም/ይነስም አንድ የጋራ ትርክት ለመሆን የሚበቃው፣ የፊውን የኢትዮጵያ ሕዝቦች ታሪክ አካቶና ተንትኖ የተፈ ታሪክ ሲኖረን ነው። የዛሬውና ው ትውልድ የጋራ ወደፊቱ የሚበራው በነገሥታቶች፣ ኤሚሮች፣ አባ ዱላዎች፣ አባ ሞጢዎች፣ ጄኔራሎችና ድርጅቶች መሪዎች… ገድል ሳይሆን የኢትዮጵያ ታሪክ ሕዝቦቿ በተጨባጭ በኖሩት ታሪክ ትርክት የደረጀ ሲሆን ነው። አቶ ታምሩ ፈይሳ ገና በ1950ዎቹ ‹‹ው ይናገር›› በሚለው ግሩም ግጥሙ

‹‹አንድ ጭብጥ ቆሎዬን ክርሽም አደርግና

አንድ ጣሳ ውዬን ግጥም አደርግና

ተመስገን እላለሁ ኑሮ ተገኘና››

ያሰኘው አትዮጵያዊ ታሪክ ሲፍና ስንስተማረው ነው። የኢትዮጵያ የታሪክ ምሁራን በዚህ ረገድ ከኢትዮጵያ ተራሮች ያላነሰ ግዙፍ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ውነተኛ ታሪክ ሥራ ከፊታቸው አለ። ያን ጊዜ ነው የኢትዮጵያን ሕዝቦች የስድስትም ይሁን የአምስት ወይም የስት ሺ ዘመን ታሪክ በውነት የምናውቀው። ያን ጊዜም ነው ዘመናትን የተሻገሩ የጋራ ትውስታዎቻችን ባለቤቶች መሆናችን የሚበራልን። የጋራ ወደፊታችንን በጋራ ለማየት የምንችለው።

ዘመናትን የተሻገሩ የጋራ ትውስታዎች ባለቤቶች ነን

በረሙ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ታሪክ ላይ ዘመን ተሻጋሪ ተማቸውን ያተሙት የኢትዮጵያ ሕዝቦች የጋራ ታሪክ በይት ንዋኔዎች ክሎድ ሌቪ ስትራውስ እንዳሉት፣ ‹‹(እነዚያ) የአጭር ጊዜ ሺ ፍንዳታዎች የተዋቸው ሺ የታሪክ ሰቆቃዎቻችንና ጠባሳዎቻችን›› አይደሉም። ይልቁንም ኢትዮጵያ የአይሁድ፣ የክርስትናና የእስልምና ሃይማኖቶችን መቀበሏና ሕዝቦቿ ሃይማኖቶቹን የየራሳቸው ማድረጋቸውስት ክፍለ ዘመን የክርስቲያንና የእስላም ኢትዮጵያ ጦርነቶች በኋላ፣ የሃይማኖቶቹ ተከታዮች በራሳቸው ጥበብ ያደረጁት ተከባብሮና ተደጋግፎ አብሮ መኖር የኢትዮጵያን አገራዊ ጠረፍ በዓለም አቀፍ ካርታ ላይ ለማተምና ለማሳወቅ የተደረጉት የጋራ ትግሎችና በተለይም የድዋው የጋራ ድል ብሔራዊ ነፃነትንና ሉዓላዊነትን ለማስከበር የተካሄደው የአምስት ዓመቱ የአርበኞቻችን የጋራ ትግልና ድል ስለዚህም በቅኝ አገዛዝ ሥር ያልወደቅን አንድ ሕዝብ መሆናችን የአፄ ምኒልክ የደቡብ ዘመቻዎችና የፊውዳላዊ ሥልተ ምርት ግንኙነት መደርጀት ለዘመናዊ ትምህርት መስፋፋትና ወደ ካፒታላዊ ሥልተ ምርት ለመሻገር የተደረጉትና የሚደረጉት ጥረቶች የአፍሪካን ኅብረት ለመገንባት የተደረጉት ጥረቶች፣ ለፊውዳላዊ ሥልተ ምርት መወገድ፣ ለሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት፣ ለፍትሕና ለኩልነት የተደረጉት የጋራ ትግሎች የሰለሞናዊውን አፄያዊ ሥርዓት በሪፐሊካዊ ሥርዓት ለመተካት የተደረጉት የጋራ ትግሎች ናቸው። ኢትዮጵያ የተበጀችው በነዚህ ሁሉ ዘመን ተሻጋሪ ክንዋኔዎች ድምር ነው። በነዚህ በሕዝቦቿ ሁሉ ድርሻ ለሺ ዓመታት በተከናወኑትና ሕዝቦቿ ሁሉ አሻራቸውን ባሳረፉበት ተቀጣጣይ፣ ተከታታይና ተያያዥ የጋራ ታሪክ ክንዋኔዎችና ጉዞ ነው።  

የኢትዮጵያ የታሪክ ልቃንና ምሁራን በዚህ ረገድ የትንቱ በዛሬው ላይ ያሳረፈውን፣ የዛሬው በነገው ላይ የሚያሳርፈውን ዘመናት ተሻጋሪ የታሪክ ማተም አበጥሮ የማውጣትና የማስተማር ግዴታ አለባቸው። ቢያንስ ከአፄ ቴዎድሮስ ዘመን ወዲህ ያለውን የታሪካችንን ክንዋኔና ደት ተቀጣጣይነት፣ ተከታታይነትና ተያያዥነት በሚያሳይና የሁሉንም ድርሻና አሻራ በሚያጎላ መንገድ ፈትፍተው ሊያቀርቡልን ይገባል። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክና የማበራዊ ሳይንስ ልቃንና ምሁራንም፣ የኢትዮጵያ ሕዝቦች የሺዘመን የፖለቲካና የማበራዊ መስተጋብሮች ያተሟቸውን የጋራ ትውስታዎች ፈልፍለውና አቀናብረው ሊያቀርቡን ይገባል። ይህ ቢፈም የብሔራዊ ማንነታችን መሠረት ፈርጥሞ ይደለድላል። የጋራ ወደፊታችን ግንባታ ማገር ጠንክሮ ይቆማል። ኢትዮጵያዊነት ሥጋ ለብሶ ይፈካልይደራል። የኢትዮጵያን ሕዝቦች የጋራ ማንነት ካበጁት ከሺዘመን መስተጋብሮችና የጋራ ትውስታዎች መካከል አንዳንዶቹን ማነሳሳት ተገቢ ነው፡፡  

ከሃዳር ሰው አፅም እስከ የመልካ ቁንጥሬ ሰውና የድንጋይ መሣሪያዎች፣ በከሊጋኡዳና የሻቤ ዋሻዎች ካሉት የእንስሳት ሥዕላት እስከ የሸዋ፣ የአሩሲ፣ የሐረር፣ የሲዳሞ ትክል ድንጋያትና እስከ ዳወሮ ግንብየቅድመ አክሱምና የአክሱማዊያን የንግድ መሰተጋብሮች ሰባተኛው ክፍለ ዘመን ለነ መሐመድ ተከታዮች የተደረገላቸው አቀባበልና መስተንግዶከአክሱም እስከ ላሊበላና ጎንደር፣ ሐረርና ያሉት ጥንታዊ ንፃዎችሐመድ ነጋሽና የሼኑር ሁሴን መካነ መቃብራትበኢትዮጵያ ምድር የደረጁት በርካታ አፄያዊ፣ ንጉሣዊ፣ ኤምራዊ፣ ልጣናዊና ሞጣዊ መንግሥታትከሰሜን እስከ ባሌ ተራሮች የቆሙት ጥንታዊ አብያተ ክርስትያናት፣ ገዳማትና መስጊዶች የደጋና ቆላ ሥልተ ምርት ዘይቤዎች ያደረጇቸው የሽማግሌ፣ የገዳ የሴራና የሄር ኢሳ ማበራዊ አስተዳደርየሰሜኑ ወገኖች ከመተማ እስከ ሞያሌና ቀብሪ ደሀር ዘልቀው የመሠረቱት የብዙ መቶ ዓመታት ኑሮየኦሮሞ ወገኖች ከባሌ እስከ ጎንደር ቤተ መንግሥት ያደረጉት ጉዞ ሁሉ የሺ ዘመን የጋራ መስተጋሮችና የኢትዮጵያዊ ማንነታችን የጋራ ትውስታዎች ናቸው። እስከ ዛሬም ያልተዘመረላቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ጀግኖች የኢትዮጵያ ብሔሮች ጀግኖች የኢትዮጵያ አርሶ አደሮችና ወዝ/ላብ አደር ያካሄዷቸው ማኅበራዊ ትግሎች፣ በኤርትራ፣ በኦጋዴንና ባድየወደቁት የመላ ኢትዮጵያ ልጆች ሲኮሩበትና ሲንቁት የማይወደው የአንድ ሕዝብ ሥነ ልቦናዊ ባሪያችን የቀረፁት የታሪክ ሁነቶች ሁሉ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ብሔራዊ መስተጋሮችና የኢትዮጵያዊ ማንነታችን የጋራ ትውስታዎች ናቸው።

የአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ትምህርትን ለማስፋፋት፣ ለፀረ ቅኝ አገዛዝና ለፀረ አፓርታይድ ትግልና ለአፍሪካ ብረት ድርጅት መመሥረት ያበረከተው አስተዋ ከተለያዩ የፖለቲካ ተዋናዮች እስከ ነዋይ ወንድማማቾች ለሪፐብሊካዊት ኢትዮጵያ የተደረገው ትግል በተደጋጋሚ የተከሰቱት የድርቅ ዓመታት ያከተሉት ዕልቂትና መፈናቀል ሁን ገሠሠ በድርቅ ላለቁት ወገኖች ‹‹ዋይ! ዋይ! …›› እያለ ባዜመው ስንኝ ከዳር እዳር ቀሰውየተማሪው እንቅስቃሴና በ60ኛው ዓመት የፈለቁት ብረ ብሔር ጅቶች ለባለ ርስት/ጭሰኛ የምርት ንኙነቶች ረዝና ለብሔር/ብሔረሰቦች መብት መታወቅና መከበር ያደረጉት የጋራ ትግልከጄኔራል ታደሰ ብሩ ስከ ዋቆ ቱ፣ ከዋቆ እስከ ወልደ አማኑኤል ዱባለ ለብሔሮች መብት መታወና መከበር የተካሄዱት ትግሎችከደደቢትና ከአርማጭሆ እስከ የግንቦት 1981 ዓ.ም. መፈንቅለ መንግሥት ሙከራና እስከ አዲስ አበባና ዳር ድንበር ድረስ የመንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ኢሠፓ አገዛዝ ለመገርሰስ የተደረጉት የጋራ ትግሎችበመንግሥት ሽብር (State Terror) ከዳር ዳር የተፈመው ፍጅት… ሁሉ የጋራ ብሔራዊ መስተጋሮቻችንና የኢትዮጵያዊ ማንነታችን የጋራ ትውስታዎች ናቸው።

እነዚህና ብዙ ያላነሳኋቸው የሺዘመናት የታሪክና የማበራዊ ተጋብሮች፣ ኢትዮጵያዊያንን አጥብቀው ያስተሳሰሩና የጋራ ማንነታችንና ምንነታችንን የገነቡና ያደረጁ ብሔራዊ ትውስታዎች ናቸው። የጋራ ብሔራዊ ንብረቶቻችንና ሴቶቻችን ናቸው። ብሔራዊ ማንነታችን ናቸው። እንዲያም ሲል ቆንጆ ፌዴራላዊ ሥርዓትንና የጋራ ወደፊታን ለመገንባት የሚያስችሉን የጋራ ጡቦች ናቸው።

የጋራ ወደፊት

አተኩረን ብንመለክት አሜሪካኖች፣ ስፓኒሾች፣ ቬትናሞች፣ ቺሊያኖች፣ ሩዋንዳዊያን፣ ሴራሊዮናዊያን፣ ላይቤሪያዊያን፣ ደቡብ አፍሪካዊያን…. እንቋጠር ካሉ ዙ የሚቋጠሩት አላቸው። ይሁንና የጋራ ወደፊታቸውን አስቀድመው (Pursuing a Shared Vision of their Future) የጋራ ቤታቸውን (ሔረ መንግሥታቸውን) በመገንባት ተጉ። እኛ ግን ከስት ሺም ይሁን ከመቶ ዓመታት በኋላ ራሱን የኢትዮጵያን መኖር/አለመኖር መጠየቅ ገባን። አሁንም አተኩረን ብንመለከት ግን በአፄ ምኒልክ፣ በአፄ ኃይለ ሥላሴና በደርግ/ኢሠፓ ዘመናት የነበሩት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በራዊ ዓብይ ቅራኔዎችና የታሪክ ጠባሳዎች በኢትየጵያ ሕዝቦች የጋራ ትግሎች በአብዛኛው ተሽረዋል። ሁለት ትውልድ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ከፍሏል። በሌላ አገላለጽ ዓብ ቅራኔ ይባሉ የነበሩት የባለ መሬት/ጭሰኛና የብሔር ቅራኔዎች በአብዛኛው ከተሻሩና ከተለወጡ ግማሽ ክፍለ ዘመን ተጠግቷል። ከአፄ ምኒልክ ዘን ጀምሮ የተተከው የባለመሬት/ጭሰኛ የምርት ግንኙነት ተሽሯል። የኢትዮጵያ ብሔሮች ባህላቸውን ማዳበር፣ በቋንቋቸው ስተማርና መፍረድ፣ ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር ከጀመሩ የአንድ ጎልማሳ ዕድሜ ሆኗል።

ይህንን ማለት ግን የተሻሩት ሥርዓቶች ቅራኔዎች ቅሪቶችና ርዝራዦች በነዋል ጠፍተዋል በዛሬው ሁኔታ ላይ ተፅኖና ጫና የላቸውም ማለት አይደለም። የተለወጡ ሥርዓቶች ቅራኔዎች ቅሪቶችና ርዝራዦች እንኳን ትንትና በተለወጠችው ኢትዮጵያ ቀርቶ አብዮታቸውን ከዛሬ መቶና ሁለት መቶ ዓመታት በፊት ባካሄዱት አገሮች ውስጥም አሉ። በእንግሊዝ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በሞናሪኪስቶችና በሪብሊካኖች መካከ የሚካሄደው ትግል እስከ ዛሬ ይካሄዳል። የፈረንይና የሩሲያ ሞናሪኪስቶችም እስከ ዛሬም አለን እንዳሉ ናቸው። የአሜሪካ የ18ኛው ክፍለ ዘመን አብዮት ከተካሄደ 250 ዓመታት ቢያልፉም፣ የነጮች የበላይነት አቀንቃሎች ቅሪት ስከ ዛሬም አልተወገደም። ይሁን እንጂ የዛሬው የየአገሮቹ ዓብይ ቅራኔዎች ምንጭ፣ የዛሬው የየአገሮቹና የዓለም አቀፍ ሁኔታዎች እንጂ የትናንትናዎቹ ቅራኔዎች ቅሪቶችና ርዝራዦች አይደሉም። የትንትናዎቹ የታሪክ ጠባሳዎች አይደሉም። ይህ ቢሆን ጀርመንና እስራኤሎች፣ አሜሪካና ትናሞች፣ የደቡብ አፍሪካ ነጮችና ጥቁሮች… በአንድ ጠረዛ የሚቀመጡበት ምክንያት የለም። ኢትዮጵያዊያንም በስ ጋዝ ከፈጇቸው ጣሊያኖች ጋራ የሚቀመጡበት ምክንያት የለም።   

1960ዎቹ ትውልድ ከ ድክመቱና ስህተቶቹም ቢሆን የባለ ርስት/ጭሰኛ የምት ግንኙነትን ታሪክ አርጎ አልፏል። የብሔሮች መብት ንዲታወቅና እንዲከበር ባደረገው ትግል፣ የኢትዮጵያን ብሔሮች ጥያቄ ከኢትዮጵያ ሞክራሲያዊ ለውጥ አጀንዳ ላይ አስቀምጦ አልፏል። ከ ድክመቱና ስህተቶቹም ቢሆን በጋራ ለመኖር የሚያስችል ፌዴራላዊ አስተዳደር ቆሟል። የዛሬው የፖለቲካ መሪዎችና ተዋናዮች ስለዚህም ለዛሬና ለነገ በበጎ የሚተርፍን ታሪክ በመሥራት እንጂ ንት በተሻሩት የትንትና ታሪክ ቅራኔዎችና ጠባሳዎች ቆፈን ቆፍድደው ቅርሾ በመቋጠር፣ በመቃቃር፣ በመናቆርና በመጋጨት የዛሬውን ትወልድ ጊዜና ሳብ የሚያባክኑበት ምክንያት የለም። ተግባርና ኃላፊነታቸው ይልቁኑ በተገኙት አዎንታዊ ድሎች ላይ ቆመው የጋራውን ወደፊት በጋራ መገንባት ነው። ጉድለቶችን አርመው የጋራውን ወደፊት ማቆንጀት ነው። በሌላ አነጋገር ብርጭቆው ግማሽ ሙሉ ነው። ተግባርና ኃላፊነታቸው ስለዚህም የቀረውን ግማሽ የሙላት ነው። ቆመው የሚገኙት ሊያባክኑት ከማይገባቸው የታሪክ አጋጣሚ ፊት ነው። በአንዱ ወይም በሌላው ፅንፈኛ ከተረቱ፣ እንኳን ለልጅ ለጆቻቸው ለነሱም የሚተርፍ ምድርና ጎጆ ባለቤት አይሆኑም።

ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በጥር አንድ ለአንድ ስብሰባ ባሰሙት ንግግርም፣ ‹‹ዕውቀት ሲንሸዋረር ገነትንም እንድንጠላው ያደርጋል›› ብለው ነበር፣ ውነት አላቸው። መምህራን፣ ምሁራን፣ ቃን፣ ጋዜጠኞች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ወላጆች፣ የምነት አባቶች፣ የብሔር መብት ተሟጋቾችና የፖለቲካ ተዋናዮች፣ . . . ሁሉ የብሔራዊ መግባባት አጎልባቾችና የጋራ ወደፊት ገንቢዎች እንጂ ‹‹የዕውቀት አንሸዋራሪዎች›› መሆን የለባቸውም ማለታቸው ይመስለኛል። ለኢትዮጵያ የሚያስልጋት ብርጭቆው ግማሽ ጎደሎ ነው እያሉ የሚያጨልሙ፣ የሚያናቁሩና የሚያጋጩ የፖቲካ ተዋናዮችን አይደለም። ብርጭቆው ግማሽ ሙሉ ነው እያሉ የጎደለውን ለሙላት የሚጥሩ የለውጥ አርበኞችን ነው። የትንቱን ጠባሳዎች አክመውና አጠግገው የነገቱን  አዲሲትና ሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ አብርተው የሚመሩ መሪዎችን ነው።

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ