Friday, December 8, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

 በውቅሮ እስከ 14 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቀው የአሚዩዝመንት ፓርክ ጅማሮ

ተዛማጅ ፅሁፎች

በትግራይ ክልል ውቅሮ ከተማ ከአሥር እስከ 14 ቢሊዮን ወጪ ሊጠይቅ የሚችል የአሚዩዝመንት ፓርክ ግንባታ መጀመሩን ባዊ ሪዞርትና አሚዩዝመንት ፓርክ የተሰኘ  ኩባንያ አስታውቋል፡፡

ኩባንያው በመቐለ ከተማ ፓርኩ ግንባታ በተመለከተ በጠራው አገር አቀፍ የውይይት መድረክ ላይ እንዳስታወቀው፣ ፓርኩ በአምስት ምዕራፎች ገንብቶ ለማጠናቀቅ መታሰቡንና የምዕራፍ አን ግንባታውም በአሁኑ ወቅት 65 በመቶ ተጠናቋል። ከኩባንያው ኃላፊዎች ማብራሪያ ማወቅ እንደተቻለው፣  ፓርኩ በሦስት ምዕራፎች የሚካሄዱ የሆቴል ግንባታዎችን ጨምሮ በርካታ የመሠረተ ልማት አውታሮችን አካቷል።

በውይይቱ ወቅትም ስለፓርኩ ዝርዝር ይዘቶች የሚያብራሩ ሦስት ጽሑፎች ለታዳሚው ቀርበዋል። ከአቅራቢዎቹ መካከል የፓርኩን የንግድ አዋጭነት የሚያማክሩት አቶ ፋንቱ ጉላ አንዱ ናቸው፡፡ አቶ ፋንቱ ፓርኩ ምን ምን የመዝናኛ ዓይነቶችን እንደሚያካትትና እያንዳንዱ ምዕራፍ ምን ያህል ወጪ እንደሚጠይቅም ለሪፖርተር አብራርዋል፡፡

ፓርኩ ሙሉ በሙሉ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ 27 ሔክታር የሚያካልል ሲሆን በምዕራፍ አን ግንባታውም በ900 ሚሊዮን ብር ወጪ ባለ ሦስትና ባለ አምስት ኮከብ ሆቴሎች የተካተቱበት ግንባታ ሥራ እንደተጀመረ ተገልጿል። መካከለኛና ከፍተኛ ገቢ ያለውን ተጠቃሚ ማዕከል በማድረግ የሚካሄደው የሆቴሎቹ ግንባታ፣ 350 ክፍሎች የሚኖሩት ባለ አምስት ወለል ሕንፃ ጽሕፈት ቤቱን አካቶ የሚካሄደው ግንባታ ሥራም ተጀምሯል።  ሰፊ መናፈሻ፣ ቢራ ፋብሪካዎች ምርቶቻቸውን የሚሸጡበት ክፍት ቦታ ወይም ቢር ጋርደን፣ ከአሥር በላይ ሙሽሮችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግድ ፏፏቴ ያለው መናፈሻ መለስተኛ ስፋት ያላቸው አዳራሾችና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ ግንባታዎች እየተከናወ  እንደሚገ አቶ ፋንቱ ገልጸዋል፡፡

​​በውቅሮ እስከ 14 ቢሊዮን

 

በምዕራፍ ሁለት የፓርኩ ግንባታ ሥራም ዋናውና ትል ዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኖረው የአሚዩዝመንት ፓርክ ግንባታ መካሄድ ይጀምራል። በዚህ ግንባታ ሒደት እንደ ዲዚላንድ ዓይነት ለሁሉም ዕድሜና ፆታ የሚመቹ የውኃ ላይ መጫወቻዎች፣ የቤት ስጥና የውጪ ጨዋታዎች ተካተዋል። በዓባይ ወንዝ አምሳያ ሰው ሠራሽ ወንዝ ታላቁ የህዳሴውን ግድ ንድፍን ጨምሮ ዓባይ ከኢትዮጵያ ወጥቶ የሚያልፍባቸውን አገሮች የሚያሳ ምስልና፣ የግብፅ ፒራሚዶችን ጨምሮ ይገነባል። አገር ውስጥና ውጭ የሚገኙ ብርቅዬ ዛፎች፣ ረዣዥም የእግር ጉዞ ለማድረግ የሚመቹ የእግረኛ መንገዶች፣ ከየትኛውም ዓለም የሚመጣ ቱሪስት በድንኳን ማረ የሚችልባቸው ቦታዎች በርካታ ተያያዥ ግንባታዎች በ1.5 ቢሊዮን ብር ወጪ እንዲገነቡ መታቀዱገልጿል፡፡

በምዕራፍ ሦስት የፓርኩ ሥራ ሒደት በ4.2 ቢሊዮን ብር በአብዛኛው የሕንፃ ግንባታ እንደሚከናወን ይጠበቃል፡፡ በአሥር ብሎክ 15 ፎቆች በአጠቃላይ 1,500 አፓርታማዎች የቤት ውስጥ መገልገያዎቻቸው ተሟልቶላቸው ለሽያጭና  ለኪራይ አገልግሎት የሚውሉ ሲሆንምህርት ቤት ሆቴል፣ ሙሉ የመዝናኛና የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራ፣ ቢዝነስ ሴንተር በግዙፉ ፕሮጀክት ውስጥ መካተታቸውን የቢዝነስ ጥና አቅራቢው አስታውቀዋል፡፡

በምዕራፍ አራት ግንባታ ሒደትም ወደ መዝናኛው ለሚመ ተጠቃሚ እንደ አቅሙ ሸምቶ የሚሄድበት የሚሊኒየም አዳራሽን ዓይነት ሰፋፊ የገበያ አዳራሾች ኤግዚቢሽን ማዕከሎች፣ ቢዝነስ ሴንተሮችና በአካባቢው የሚመረቱ ምርቶችን ቀጥታ ገበሬው አምጥቶ የሚሸጥበት ሥፍራ የተዘጋጀለት ሲሆን ከቢዝነስ ጋር የተያያዙ ሌሎች ግንባታዎች በዚህ ምዕራፍ እንገነቡ ዕቅድ መያዙን አስቀምጠዋል፡፡

በምዕራፍ አምስ የፕሮጀክቱ ክፍል፣ ሙሉ በሙሉ በባለቤቱ ሐሳብ አመንጪነትና በአሚዩዝመንት ፓርኮች ያልተለመደ ተብሎገለጸው አቶ ንቱ ያቀረቡት፣ ትልቋን ኢትዮጵያ በአንድ ማዕከል በማምጣት የአንድ ኢትዮጵያ ተምሳሌ የሚወክል ማሳያ ማዕከል መገንባት ነው። ለዚህም ዩኔስኮ የመዘገባቸው በኢትዮጵያ የሚገኙ ኪነ ሕንፃዎች በተለይም አክሱም ሐውልት፣ ፋሲል ግንብ፣ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትና ሌሎችም ሕንፃዎች በውስጣቸው ሆቴሎች ሙዚየሞች የስብሰባ አዳራሾች እንደሚገነቡ ጠቅሰው 50 ሎጆች በኢትዮጵያ ባህልና ቅርስ መሠረት በፕሬዚዳንሺያል ስዊት ደረጃ ለመገንባት ዝግጅቶች እንተጠናቀቁ ገልጸዋል፡፡

አቶ ግርማይ ኃይሌ ከዚህ ሁሉ ፕሮጀክት ጀርባ ያሉ ባለሀብት ናቸው። ተወልደው ያደጉት በውቅሮ ከተማ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በንግድ ሥራ የሚተዳደሩና የዋው ፈርኒቸር ድርጅት ባለቤት ናቸው፡፡ አቶ ግርማይ የዚህ ሐሳብ አመንጪና ባለቤት ናቸው፡፡ ስለ ፓርኩ አመሠራረትና ሒደት ለሪፖርተር እንደገለጹት ሐሳቡን ስምንት ዓመጀምሮ ሲያውጠነጥኑት ቆይተዋል፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚሳተፍበት አገራዊ ልቋን ኢትዮጵያ በአንድ ማዕከል በማሳየት የአንድነትን ተምሳሌት መገንባት አንዱ ዓላማቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣ ቱሪስት ውቅሮን እንደልቡ ተዘዋውሮ እንዲመለከት እንዲዝናናና ያስችለዋል በሚል ሐሳብ ፕሮጀክቱ መጠንሰሱን ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ ጥናት ሲጀመር ግን ሌሎ ሐሳቦችም እንደተፈጠሩ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

አቶ ግርማይ እንደሚሉት እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶች ለኢትዮጵያ አዲስ ግዙፍ ስለሆኑ የመሳካት ዕድላቸው አነስተኛ ነው ሲባል ንደሚሰሙና እሳቸውም ስለፕሮጀክታቸው ይህንኑ እንደሚጠየቁ ገልጸው፣ እኛ ዓመታት የፈጀ ጥናት በማድረ ሚገጥሙን ችግሮች መፍቻ ዕቅድ ጭምር ወረቀት ላይ ጨርሰን ነው ወደ ሥራ የገባነው ብለዋል። በመሆኑም ፕሮጀክቱን ለማሳካት ግንባታው መካሄድ ያለበት ደረጃ በደረጃ እንደሆነ ጥናቱ ማመላከቱን ጠቅሰው፣ ምዕራፍ አንዱ ግንባታም ጥራቱን ጠብቆ በአንድ ዓመት ጊዜ ለሕዝብ ክፍት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

 ፕሮጀክቱ የሕዝብ ስለሚሆን በውቅሮ ከተማ ስለፓርኩ ግንባታ ሒደት የተካሄደውን ዓይነት ሕዝባዊ ውይይት፣ በመጪው መስከረም 2012 ዓ.ም.  በአዲስ አበባ ከሁሉም ክልሎች ፌደራል መንግሥት የተውጣጡ አካላት ሐሳብ የሚሰጡበትና የባለቤትነት ድርሻውንም ለሚመለከታቸው ሁሉ የማከፋፈል ውጥን የተያዘ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ዕውን እንደሚሆን ያላቸውን ሐሳብ ገልጸዋል፡፡

አሚዩዝመንት ፓርኩ በውቅሮ ከተማ በሊዝ በተገኘ መሬት ላይ ግንባታው እየተካሄደ ይገኛል። ፕሮጀክቱን የሚከታተሉ የግንባታ፣ ገንዘብ አፈላላጊ፣ የግዢ አገልግሎት የሚሰጡ ኮሚቴዎች ተዋቅረውለት ሥራውን ተከፋፍለው እያካሄዱት ይገኛሉ፡፡ ለ1,500 ለአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል የፈጠረው ይህ ፕሮጀክት፣ ለፓርኩ ግንባታ የሚውል ውኃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተደርጎ እስካሁንም ሁለት ጉድጓዶች ተቆፍረው ለሥራ ዝግጁ ተደርገዋል። ግንባታው ተጠና ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት እስኪጀምር ወደ ቋሚ አገልግሎት ሰጪነት ከገባም በኋላ ከአሥር ሺሕ በላይ ሠራተኞች የሚያስፈልጉት ፕሮጀክት፣ ከወዲሁ ከግንባታው ትይዩ ሠራተ የመመልመልና የማሠልጠን እንቅስቃሴም እያካሄደ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ደፊት ፓርኩ በአክሲዮን ድርጅት መተዳደር በሚችልበት መንገድ እንደሚደራጅ ተጠቅሷል። ባለሙያዎች ስብስብ ቦርድ አመራሮች በተጨማሪ፣ አማካሪ ቡድን እንደሚኖረውም ተገልጿል፡፡ አሚዩዝመንት ፓርኩ ከተጠናቀቀ በኋላ እንደ የአገልግሎት አሰጣጣቸው ልምድ ላላቸው የውጭ አስተዳዳሪዎች የሚሰጥ ሲሆን ይህን የማድረጉ ሒደትም ከስምንት እስከ አሥር ሳምንት ይፈጃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አቶ ግርማይ የፋይናንስ ምንጩ ከየት እንደሆነ፣ ምን ያህሉ እስካሁን እንደተገኘ ሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹ጥናቱ ይህንንም ከመነሻው የመለሰው ጥያቄ ሲሆን፣ ከአገር ውስጥና ከውጭ ባንኮች፣ አብረውን ለመሥራ ከተስማሙ አሜሪካ እንግሊዝ ቱርክ ባለሀብቶች የሚገኝ ነው፤›› ካሉ  በኋላ ምሳሌነት የጠቀሱትም፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ ግንባታ ለማካሄድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡ ‹‹እነዚህ ባለሀብቶች አብረውን ለመሥራት መንግሥት በፕሮጀክቱ ላይ ያለውን እምነት ጠይቀውን ይህንንም እየጨረስን ሲሆን፣ እሱን እንዳገኘን ተፈራርመን በቀጥታ ወደ ሥራው ስለመግባት የገንዘብ ችግር ይገጥመናል ብለን አናስብም፤›› ብለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች