Tuesday, November 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ

ቀን:

ነባሩን የሕወሓት አመራር አባል አቶ ብርሃነ ኪዳነ ማርያምን ከሁለት ዓመት በፊት በመተካት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሸን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ሥዩም መኮንን፣ ማክሰኞ ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ለሠራተኞች አስታወቁ፡፡

አቶ ሥዩም ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ያሳወቁት የኮርፖሬሸኑን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም አስመልክቶ፣ በኢትዮጵያ ሆቴል ከሠራተኞች ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው፡፡ ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ሲገልጹ የስብሰባው ተሳታፊ የነበሩ ሠራተኞች በከፍተኛ ጭብጨባ የድጋፍ ይሁን ወይም የተቃውሞ ባይታወቅም ስሜታቸውን መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

አቶ ሥዩም ከተሾሙበት ወርኃ ነሐሴ መጨረሻ 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ኮርፖሬሽኑን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የተለያዩ ለውጦችን ማምጣታቸው ቢወሳም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተቃውሞዎች እንደነበሩባቸው ይነገራል፡፡

እሳቸው በሚዲያው ዘርፍ የተሻለ ዕውቀት ያላቸው መሆናቸውን አብረዋቸው የሠሩ ይመሰክሩላቸዋል፡፡ የአማራ መገናኛ ብዙኃን ቢሮ ኃላፊ፣ እንዲሁም በአማራ ክልል የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳዳሪ ሆነው ሠርተዋል፡፡ ከጥቂት ጊዜ ወዲህ አቶ ሥዩም በሥራቸው ላይ ተፅዕኖ እንደሚደርስባቸው በሚያስታውቅ ሁኔታ አባል ለሆኑበት የፖለቲካ ድርጅት የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)፣ ከኃላፊነታቸው ለመልቀቅ በተለያዩ ጊዜያት ጥያቄ ማቅረባቸውን ምንጮች ይናገራሉ፡፡

ነገር ግን አቶ ሥዩም በፖለቲካ ድርጅታቸው ወይም በሌላ አካል ግፊት ይሁን ባይታወቅም፣ እስከ ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ድረስ ሲመሩት የቆዩትን ኢቢሲ ኃላፊነት መልቀቃቸውን ያሳወቁ ቢሆንም፣ ዝርዝር ምክንያታቸውን ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት በ1994 ዓ.ም. ያገኙት አቶ ሥዩም፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ አሜሪካ ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡

ኢቢሲ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዳዲስ የቦርድ አባላት ሲመደቡለት፣ ቦርዱን በኃላፊነት እንዲመሩ የተመረጡት የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዴፓ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ፍቃዱ ተሰማ መሆናቸው ይታወሳል፡፡

አቶ ሥዩምን ከኃላፊነታቸው የለቀቁበትን ምክንያት ለማወቅ ሪፖርተር ጥረት ቢያደርግም፣ ኅትመት እስከሚገባ ድረስ ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ማግኘት አልተቻለም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...